Translate

Monday, January 31, 2022

#ጀቡቲ የማን ነበረች/ Djobouty

የኢትዩጵያ ግዛት አካል ለነበረችው ጂቡቲ መገንጠል ማን ነው ተጠያቂው ??????? https://www.facebook.com/wallo.lion.9 ጂቡቲ እስከ 1897 ድረስ የኢትዩጵያ ግዛት አካል ስትሆን በተለይም የኢፋትና አዳል ሙስሊም ሱልጣኔቶች ዋና የባህር በር እና መቀመጫ ስትሆን የእስልምና ሃይማኖት ወደ መሃል ሃገር እንዲገባና እዲስፋፋ ትልቅ ቦታ ነበራት ። ከ13ኛው ክፍለ ዘመን እስከ 16ኛው .ክ.ዘ የክርስቲያን መንግስት በኢማም አህመድ ኢብን ኢብራሂ አልጋሃዚል በመጨረሻ በ1529 እሲኪሸነፍ ድረስ ዋና የሃገሪቱ የባህር በር ነበረች ። እንዲያውም በተደጋጋሚ በክርስቲያን ነገስታት እነ አምደፂዎንና ዘርያቆብ እና በሙስሊም ሱልጣኔት መካከል የነበርው ፍልሚያና ጦርነት ይህንን ዋና የባህር በር ንግድ ለመቆጣጠር ነበር ። እንደሚታወቀው የጂቡቲ ህዝብ ከአፋር ፣ከሱማሌው ፣ከሃደሬ ፣ከአርጎባና ኦሮሞ በተወሰነ የዘር ሃረጉ ይመዘዛል ። ሌላው ይቅርና ግብጻዊያን የጂቡትን እስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ በመርዳት የጥንቱን ኦቦክና ታጁራን (የአሁኑን ጂቡትን ) ለመውረር ብዙ ጥረት አድርገዋል፣ በኃላም በዚሁ በኩል አድርገው ነው ሃረርንም ለመውረር የሞከሩት ። በዋናነት ፈረንሳይ የአሁኗ ጂቢቲ ለመውረር ፍላጎት ያሳየችው ገና በ1860 መጨረሻ ጀምሮ ነው ። በመቀጠልም ግዛቴ ነው የሚል አዋጅ አስነግራ ጂቡቲን እንደ አንድ ግዛቷ ማስተዳደር ጀመረች በመጨረሻም በ1897 ከሚኒልክ ጋር በመስማማት የኢትዩጵያና ጅቡቲ የደንበር ወሰን ተካለለ ። ይህ ስምምነትም እንደገና ፈረንሳይ ከኃይለስላሴ ጋር በ1945 እና 1954 ዓ.ም ዳግም በውል ስምምነት ፀና ። ከእነዚህ የውል ስምምነቶች በኃላ ጅቡቲ ራሷን የቻለች በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ያለች ሃገር ሆነች ። በመጨረሻም በ1977 ሉአላዊ ሃገር ሁና ከእናት ሃገር ኢትዩጵያ ተገንጥላ ራሷን ችላ ተመሰረተች ። እስኪ ይህንን የሚከተለውን ታሪክ አንብቡት ።

No comments:

Post a Comment

mootittii saba'a Queen of sheba

"Mootittii Saba'a""Queen sheba" ----------------------------------------------------------------- ★Miky Sultan Bar...