The history chamber of the ancient african people Ham the sons of noah/ Kush,canaanite civilizition
Seenaa ilma nuuh "Ham " Abbaa afrikaa qaroomina kush & kana'an የኖህ ልጅ ታሪክ ሃም የአፍሪካ አባት የኩሽ እና ከነዓናዊ ስልጣኔ! For those who want to learn more about the history, culture, way of life, and civilization of the Cushites, visit our website.https://mikysultan.blogspot.com
Translate
Tuesday, September 8, 2026
ንጉሥ ሙሀመድ አሊ
👑🔥 ንጉሥ ሙሀመድ አሊ (አባ ሻንቆ) ዘበሔረ ወሎ — የወሎ አንበሳ! 🔥👑
★ Miky Sultan Barento ★
“ሻንቆ” የፈረስ ስማቸው ነው፤ ጀግንነትን ያሳያል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
🌿 የወሎ ኦሮሞ የቤት አሊ ታሪካዊ የውልድ ሐረግ 🌿
ወልዳቸው ከወሎ ኦሮሞ፣ በወረ ሒመኖ የተዋቀረው የቤት አሊ የትውልድ መስመር፦
🌿 ባሬንቱማ
⬇️
🌿 ወሎ — ወረ ሒመኖ
⬇️
ባቦ
ጎዳና
⬇️
አሊ
⬇️
ሙሐመድ (አባ ጀቦ / ጅቦ)
⬇️
አመዴ
⬇️
ሊበን (አባ ጅሩ)
⬇️
👑 ሙሐመድ አሊ (አባ ሻንቆ)
📜 ሙሐመድ (አባ ሻንቆ) → አሊ (አባ ቡላ) → ሊበን (አባ ጅሩ) → አመዴ (ኮላሴ) → ሙሐመድ (አባ ጀቦ/ጅቦ) → አሊ → ጎዳና → ባቦ የሚሉትን የውልድ ስሞች የሚያገናኝ ሙሉ የትውልድ መስመር ነው።
👑 ልጃቸው፦ ኢያሱ ሙሐመድ አሊ
ሊበን → አመዴ → ሙሐመድ → አሊ → ጎዳና → ባቦ
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
👑🔥 ንጉሥ ሚካኤል ዘበሔረ ወሎ 🔥👑
የወሎ ታሪክ ሲነሳ፣ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻና በ20ኛው መጀመሪያ ዘመን በጥልቅ የሚጠቀሱት ሰው ንጉሥ ሚካኤል ዘበሔረ ወሎ ናቸው።
በልደታቸው ስም መሐመድ አሊ ይባሉ ነበር። አባታቸው አሊ አባ ቡላ የወሎ የማመዶች ቤተሰብ መሪ ነበሩ።
መሐመድ አሊም የአባታቸውን የሥልጣን ውርስ ለማስመለስ ከልጅነታቸው ጀምሮ የረጅም ጊዜ ትግል አደረጉ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
⚔️🔥 የወረ ሒመኖ የሥልጣን ትግል 🔥⚔️
በወቅቱ የወሎ ፖለቲካ በተለያዩ የባላባት ቤተሰቦችና ገዥዎች መካከል በጣም የተወሳሰበ ነበር።
መሐመድ አሊ የአባታቸው ሥልጣን ለእሳቸው እንደሚገባ በመከራከር የሥልጣን ትግል ጀመሩ።
በዚህ ትግል ውስጥ አመዴ ሊበን (አባ ዋጠው) የተባሉት የወሎ ኃይለኛ መሪ ከመሐመድ አሊ ጋር ዋና ተቀናቃኝ ሆኑ።
📜 የወሎ ሕዝብ ለመሐመድ አሊ ያሳየው ድጋፍ በባህላዊ ቃል እንዲህ ተገልጿል፦
««አሞራ ገደል ላይ አንበሳ አስሬ፤
እርሱ ቢበጥስም እኔም አብሬ!»»
ይህ ቃል የወቅቱን የሕዝብ ድጋፍና የትግሉን ጥንካሬ የሚያሳይ ትውፊታዊ አገላለጽ ነው።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
በቦሩ ሜዳ በ አፄ ሚኒሊክና በ አፄ ዩሃንስ ተሸንፎ በግድ ክርስትና ተንስቶ
✝️ መሐመድ አሊ ወደ “ሚካኤል”
በ1878 የቦሩ መዳ ጉባኤ ላይ
መሐመድ አሊም ክርስትናን ተቀብለው “ሚካኤል” የሚል የክርስትና ስም አገኙ።
ከዚያ በኋላ ራስ ሚካኤል በሚል ስም በመላው ኢትዮጵያ ታወቁ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
🏛️🔥 ደሴና የወሎ አስተዳደር
ሚካኤል የወሎን አስተዳደር ሲያጠናክሩ፣ ደሴ የአስተዳደር ማዕከል እንድትሆን ትልቅ ሚና አበረከቱ።
ዛሬ ደሴ የወሎ ዋና ከተማ ሆና መታወቋ ከዚህ የታሪክ ሂደት ጋር በጥብቅ የተያያዘ ነው።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
⚔️🇪🇹 አድዋ — 1896
ንጉሥ ሚካኤል በ1896 የአድዋ ዘመቻ የወሎ ኃይሎችን በመምራት በኢትዮጵያ የድል ታሪክ ውስጥ ቦታ አላቸው።
የወሎ ፈረሰኞችና ተዋጊዎች በአድዋ ዘመቻ ውስጥ የተሳተፉ ሲሆን፣ ይህም የወሎ ወታደራዊ ኃይል በዚያን ዘመን የነበረውን ጠንካራ ሚና ያሳያል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
👑 የኢያሱ አባት — የመነን አያት
ንጉሥ ሚካኤል የልጅ ኢያሱ አባት ናቸው።
የልጅ ኢያሱ ቤተሰብ ከኢትዮጵያ ንጉሣዊ ቤት ጋር በተገናኘ ጊዜ የወሎ ቤተሰብ የንጉሣዊ ቤተሰብ አካል ሆነ።
ወይዘሮ ስህን የንጉሥ ሚካኤል ልጅ ሲሆኑ፣ በእሷ የዘር መስመር ንጉሥ ሚካኤል የእቴጌ መነን አያት ይሆናሉ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
🔥👑 ንጉሥ ሚካኤል ዘበሔረ ወሎ
በወሎ ታሪክ ውስጥ ብቻ የሚታወሱ መሪ አልነበሩም።
ከወሎ የሥልጣን ትግል፣ ከሸዋና ትግራይ የነበረው የዘመኑ ፖለቲካ፣ ከአድዋ ዘመቻ እና ከኢትዮጵያ ንጉሣዊ ቤተሰብ ታሪክ ጋር የተሳሰሩ ታላቅ ታሪካዊ ሰው ነበሩ።
🔗 https://mikysultan.blogspot.com
🔗 https://t.me/Oromo_geography
👑🔥 የወሎ ታሪክ ሲጻፍ፣ የንጉሥ ሚካኤል ስም መታለፍ የለበትም! 🔥👑
#ንጉሥ_ሚካኤል
#መሐመድ_አሊ
#አባ_ሻንቆ
#ወሎ
#ወረ_ሒመኖ
#ደሴ
#አድዋ
#ልጅ_ኢያሱ
#እቴጌ_መነን
#የወሎ_ታሪክ
#MikySultanBarento
“ኢትዮጵያ” የሚለው
🇪🇹🔥 “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃልም ከጎንደርና ከጎጃም ሰዎች አፍ ላይ አይወጣም 🔥🇪🇹
★ Miky Sultan Barento ★
ልብ አንለውም እንጂ “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃልም ከጎንደርና ከጎጃም ሰዎች አፍ ላይ የተለመደ አይደለም፤ “ጎንደር፣ ጎጃም” ስለሚሉ ብቻ ኢትዮጵያ ያሉ ይመስለናል እንጂ “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃል በግድ ነው ከአፋቸው የሚወጣው፤ ይህ እየሆነ ያለው ታዲያ በኢትዮጵያን ፈጣሪው ላይ /በሀገር ማቅናቱ ላይ/ እንደሌሉበት ስለሚያውቁ ነው።።
⚠️ ይህ ተከታሎ ጎንደርና ጎጃም ውስጥ ባህል እየሆነ የመጣ አደገኛ ነገር አለ፤
በአካባቢያቸው ማህበረሰብ ዘንድ እንደእነኚህ አይነት ነገሮችን ማሳየትን እንደ ስልጣኔና ጀግንነት የመቁጠር ባህል አለ፤ ይህ ባህል ለሀገሪቱ እጅግ ጎጂ ነው እናም ግልፅ መውጣት አለበት ነው እያልን ያለነው።።
🎵 ለምሳሌ ያህል፤
ጎጃም ውስጥ ከንዋይ ደበበ የበለጠ ጀግና የለም፤ ምክንያቱም ደግሞ ደስ በሚልና በግድ ጆሮ ውስጥ በሚገባ ዜማ “ጋምቤ ላይ ጋምቤ”፣
«“እንገዲህ ጎጃም ላይ ምን ተሰራ አትበሉ፤
ታሪክ ጠይቃችሁ በላይ በላይ በሉ”»
በሚለው ዘፈኑ የበላይ ዘለቀን ታሪክ ከወሎ በመንጠቅ ነው።።
ቀደም ሲልም እንደምሳሌ “የዜማ የቅኔ የቀሳውስት ሀገር” የሚለውን የንዋይን ዘፈን አይተናል፤ በዚህ ዘፈን ውስጥ የአፍሪካ ትልቅ ቅርፅ ላሊበላ አልተጠቀሰም፤ በሚገርም ሁኔታ “ፋሲለደስ አክሱም የታሪክ ምስክር” ሲል ፋሲለደስም የሸዋ ሰዎች ቅርፅ እንደሆነ ዘፈኑ አሳምሮ ያውቃል /ህዝቡ ታሪኩን እንደማያውቅና እንደተደነገበረ ስለሚያውቅ ነው ፋሲለደስን የጎንደር ቅርፅ ለማስመሰል “አክሱም ላሊበላ” በማለት ፋንታ “ፋሲለደስ አክሱም” ያለው/።።
ይህ እንግዲህ ምን ያህል የወሎ /የኢትዮጵያ/ ታሪኮች ከአፋቸው እንደማይወጡና የኢትዮጵያ ታሪኮችንም በምን አይነት ስልት ወደ እነሱ እየቀየሯቸው እንደሆነ ያሳያል።።
---
🔥 ይህ በአጠቃላይ የጎንደርና ጎጃም ባህል ነው፤
ጎንደርና ጎጃም ውስጥ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ጀግና የምትባለውና የምትሞገሰው እንደዚሁ የወሎን ስም አጥፍተህ ታሪኩን ያንተ አስመስለህ ለህዝብ ያደረስክ እንደሆነ ነው።።
ይህ ሁኔታ በየጊዜው የኢትዮጵያን ታሪክ እያጠፋና የአጼ ቴዎድሮስና የበላይ ዘለቀ ታሪክ ብቻ እያሰመሰለው ቀጥሏል።።
ሌላውና ዋናው ጎንደርና ጎጃም የኢትዮጵያን ታሪክ ለመቀየር የሚከተሉት ስልት የወሎን ተፈጥሮ እንዳልወደዱት በማስመሰል የወሎን ስም ማደብዘዝ ነው፤ ነገር ግን እውነታው ሌላ ነው /ወሎን ጠልተው አይደለም፤ ምክንያቱም ለምሳሌ ያህል፤ የጎጃሙ ጀግና ንዋይ ለሐረር ዘፍኗል፤ የሐረርና የወሎ ህዝብ ተፈጥሮ ደግሞ አንድ አይነት ነው፤ የወሎና የጉራጌ ህዝብ ተፈጥሮም አንድ አይነት ነው።።
ስለዚህ ወሎን ጠልተውት ሳይሆን ታሪኩ ግልፅ እንዳይወጣ ስለፈሩ ነው ማለት ነው።
---
📚 የኢትዮጵያ ታሪክ የማን ነው?
የሆነም ደግሞ ይህ እነሱ የፈጠሩት ስልት እነሱን ብቻ የኢትዮጵያ የታሪክ ባለቤት ሊያደርጋቸው አይገባም፤ ሌሎች ከእነሱ እጅግ የተሻለ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ተሳታፊ የነበሩት ብሔረሰቦችም የኢትዮጵያ ታሪክ ባለቤት መሆን አለባቸው /ወሎ የሁሉም ብሔረሰቦች ድብልቅ ነው/።።
ይህ የሚሆነው ታዲያ በታሪክ ስነፅሁፍና በታሪክ የዘፈን ስራ ውስጥ ሌሎች ብሔረሰቦችም ተሳታፊ ከሆኑና የኢትዮጵያን ትክክለኛ ታሪክ በየጊዜው ለህዝብ ማድረስ ከተቻለ ብቻ ነው።።
ይህ ግን እየሆነ አይደለም፤ ይህ የማይሆንበት ዋናው ምክንያት ደግሞ አንዳንድ ብሔረሰቦች የሚያዩት የሚነገረው ቋንቋ አማርኛ መሆኑን ነው፤ ይህ እጅግ ስህተት ነው፤ ቀደም ሲል እንዳየነው አማርኛ ቋንቋ ከመምጣቱ በፊት የጎንደሬዎችም ቋንቋ ጋፋትኛ፣ ዛይኛና ቅማንትኛ ነበር።።
ግዕዝ /አረብኛ/ ተናጋሪዎች ደግሞ በዙሪያችን ያሉት ሀገሮች አረብ በመሆናቸው ነው፤ /አረብ ocean ውስጥ ስለምንገኝ ነው/።።
ቀደም ሲል እንዳየነው አማርኛ ቋንቋ የማንም ያልሆነ የወታደሮች ቋንቋ ነው፤ አረብኛው ከየመን መጥቶ ትግራይ ውስጥ ወደ ግዕዝነት ተቀየረ ከዚያም ላስታ /አጋው/ ውስጥ በወታደሮቹ አማካኝነት ወደ አማርኛ ተቀየረ።።
ስለዚህ አረብኛ መናገራችንን ሳይሆን ታሪካችንን ነው ማየት ያለብን ማለት ነው።።
አብዛኞቹ ጎንደር ላይ ያለው አጼው ቤተመንግስት የሸዋዎች መሆኑን እንኳ ስላማያውቁ የጎንደርን ቤተመንግስት በቴሌቪዥን ሲያዩ የኢትዮጵያ ታሪክ የማይመለከታቸው ስለሚመስላቸው ወደ የታሪክ ዘፈን ስራና የታሪክ መፅሐፍት ድርስ /ዝር/ አይሉም ።።
ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው ነው የኢትዮጵያን ታሪክ እያበላሹት የቀጠሉት።
---
🤝 ለቀጣይ ትውልድ የምናስቀምጠው ታሪክ ምን ይሁን?
እናም ሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ ይህን የጎጃምና የጎንደርን ማህበረሰብ የመሞገስ ባህል መከላከል፤ በስነፅሁፍና በዜማ የኢትዮጵያን ትክክለኛ ታሪክ በየጊዜው ለህዝብ ማድረስ አለባቸው ማለት ነው።።
ለቀጣይም ትውልድ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ታሪክ አስቀምጦ ማለፍ ከሁሉም ብሔረሰቦች ይጠበቃል ማለት ነው።።
🇪🇹 ወደ ርዕሳችን ስንመለስ፦
በጣሊያን ዳግም ወረራ ጊዜ እንዳየነው እነዚህ በግንዛቤ ችግር የተፈጠሩ ቅሬታዎች ግልፅ ካልወጡ በስተቀር ውስጥ ውስጡን የሀገሪቱን ታሪክ ማጥፋት ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱንም አንድነት ችግር ውስጥ ሊከተው ይችላሉ።።
ሸዋናወሎ በጎጃም ላይና በተለያዩ አካባቢዎች ላይ የፈፀሙት ድብደባ የሀገር ማቅናቱ /ማስፋፋቱ/ አካል እንጂ ቅሬታ የሚያስከትል ነገር አይደለም።።
ሸዋና ወሎ አዋቂዎች እንደዛ ባያደርጉ ኖሮ ይህች የምትባል እጅግ ሰፊ በተፈጥሮ የበለፀገች ሀገር አትኖረንም ነበር ማለት ነው።።
ስለዚህም ከዚህ ያረጀ አስተሳሰብ ከፈጠረው ኋላቀር አመለካከታችንና ጭፍንነታችን መውጣት ይኖርብናል ማለት ነው።።
በአረጀ አስተሳሰብና ጭፍንነት ምክንያት የተፈጠረው የጎጃሞች ቅሬታ እያሰከተለው ያለው ጥፋት ያየነውን ሲመስል የወለጋዎች ቅሬታ ግን በወቅቱ የሀገሪቱ አጠቃላይ ችግር ከነበረው ከባሪያ ንግድ ጋር የተያያጠና በተጨባጭ ተፅዕኖ የማይገኝ የመንደር ወሬ ነው፤፤
ስለዚህም በተጨባጭ ተፅዕኖ በማይገኝ የመንደር ወሬዎች ላይ ተመስርቶ መፃፍም ሆነ ዘፈን መስራት አይቻልም ማለት ነው /ወሬዎች አላማቸው ይለያያል/።።
ስለዚህም የወለጋ ቅሬታ ተፅዕኖ የማይገኝምና የወቅቱን ሁኔታ እንኳን ለማወቅ የመጣ እጅግ ያረጀ አስተሳሰብና ኋላቀር አመለካከት የወለደው ቅሬታ ነው /conservativeness የወለደው ቅሬታ ነው ማለት ነው/።
ከዚህም በተጨማሪ ያች ቀደም ሲል ያጠናት ከጊቤ ወንዝ ጋር የተያያዘችው ቃልም በወለጋዎች ዘንድ ቅሬታ ሳይፈጥር አይቀርም።
እናም ኢትዮጵያ ውስጥ ካለማንበብና ታሪክን ካለማወቅ ጋር የተያያዙ በርካታ ችግሮች አሉ ማለት ነው።።
https://mikysultan.blogspot.com
🔗 https://t.me/Oromo_geography
🇪🇹📚 ታሪክ በማንም አካባቢ ብቻ የሚወሰን አይደለም፤ ምንጩ ተመርምሮ ለትውልድ መተላለፍ አለበት።
#ኢትዮጵያ #ወሎ #ጎጃም #ጎንደር #ሸዋ #ወለጋ #ታሪክ #የኢትዮጵያ_ታሪክ
Monday, September 7, 2026
የእምባቦ ጦርነት
🔥⚔️ የሸዋ ወሎና የጎጃም ጦር ግጥምያ ⚔️🔥
ጎጃሞች ዘራፍ አበዙ የወሎ ሰው ዘምቶ አፉን አስያዘው
📜 የእምባቦ ጦርነት (Battle of Embabo)
★ Miky Sultan Barento
🕔 ከቀኑ 5 ሰዓት
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
የጎጃሞቹ ጦር መድፍ መተኮስ ጀመረ። የወሎ ጦረኞችም ወደ ጦርነቱ ተጠግተው ውጊያ ገጠሙ።
ንጉሥ ሚኒሊክም አሽከሮቻቸውን ይዘው መሀል ለመሀል ገቡ። በዚህ ጊዜ የጎጃሙ ንጉሥ ተክለሃይማኖት መድፍ መተኮስ ጀመሩ።
💥 መድፉን ሁለት ጊዜ ተኮሱ። በሦስተኛው ግን መንኩራኩሩ ተመቶ ተሰብሮ ወደቀ።
የጎጃም ጦርም የጦርነቱን ሁኔታ ባየ ጊዜ ደነገጠ።
⚔️ የወሎ ጦር ተጣጥፎ ከቦ አጨናነቀ።
ከሁለት ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ፣ ንጉሥ ተክለሃይማኖት ቆስለው ተማረኩ፤ የወሎ ጦርም ይዟቸው መጣ።
ጦርነቱ ግን እስከ 3 ሰዓት ድረስ ቀጠለ። የወሎ ጦር ከበቡት፤ የጎጃም ጦርም ለመሸሽም ለመማረክም የማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ገባ።
በጦርነቱ ብዙ ሰዎች ከወደቁ በኋላ፣ የጎጃም ጦር ሙሉ በሙሉ እጅ ሰጠ፤ ጦርነቱም ተጠናቀቀ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
📜 ከዚህ በኋላ የወሎን ስም የማጥፋት ዘመቻ መነሻው ይህ ጦርነት ነው ተብሎ በታሪክ ትውስታ ይነገራል።
🔥 የወሎ ታሪክ ይታወስ!
📜 ታሪክ አይጥፋ!
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#የእምባቦ_ጦርነት
#የወሎ_ታሪክ
#ወሎ
#ጎጃም
#ሸዋ
#MikySultanBarento
የቴዎድሮስ ዙፋን ምስጢር
🔥👑 የቴዎድሮስ ዙፋን ምስጢር — እቴጌ ተዋበች ባትኖር ቴዎድሮስ አይነግስም ነበር?
አፄ ቴውድሮ የራስ አሊ የጁ አሽከር ነበረ
ተዋበች ባትኖር ቴድሮስ አይነግስም ነበረ
ተዋበች ባትኖር ቴዎድሮስ አይነግስም ነበረ
ራስ አሊ አሉላ (Ali II of Yejju)
⬇️
እቴጌ ተዋበች ራስ አሊ አሉላ መርሶ ባሬንቶ
⬇️
አያቷ፦ እቴጌ መነን ሊበን አመዴ
በእናቷም በ አባቷም የባለባት ልጅ ነበረች።
★ Miky Sultan Barento ★
📜 ወደ ጋዜጠኛ ፍስሐ ስንመለስ፦
“ቅድም ነገሩ ሁሉ ከቁጥጥራቸው ውጪ እየሆነ ሲመጣ ቁጣቸው ገነፈሎ አሁንም ካህናቱን እጣን ጠባሽ፤ ፊሰ ሰፊ፤ ራሱን ታጣቂ፤ ወገቡን ስባቂ... እያሉ ይዘልፏቸዉ ጀመረ፡፡ በርካቶችን ወደ ገደል አስወረወሯቸዉ፡፡ ብዙዎችንም እሳት እንዲነድዉ ወደ እሳት ጨመሯቸዉ፡፡ የቀሩትንም በጦር አስወጓቸዉ ይላል፤
ይህን ሁሉ ግፍ በካህናቱ ላይ ቢፈፅሙም የመሳፍንቱ አመፅ እንኳን ሊቆም እየባሰበት ሄደ፡፡ አፄ ቴዎድሮስም አመፁን መቋቋም ተሳናቸዉና የጎንደር ቤተመንግስትን ለመልቀቅ ተገደዱ፡፡ እቃቸዉን ጠቅልለዉ ይዘዉ ሄደዉ መቀመጫቸዉን ደብረ ታቦር አደረጉ” ይላል፡፡
---
⚔️ የዋግሹም ጎበዜ መነሳት
ከዚህ በኋላ የሀገሪቱ የፖለቲካ ቁልፍ የቆቀመዉ ዋግሹም ጎበዜ /በኋላ አፄ ተክለጊዮርጊስ 2ኛ/ እጅ ውስጥ ገባ፡፡
ቴዎደሮስ ደብረ ታቦር ሲያፈገፍግ ሁሉም የጦር መሳሪያና አሰራሮችን ይዞ ነበር፡፡ ዋግሹም ጎበዜም /በኋላ አፄ ተክለጊዮርጊስ 2ኛ/ ቴዎድሮስን ዙሪያዉን ከቦ እየተከታተለ ግዛቶቹን ሁሉ ነጥቆ በደቡብ ወሎ መቅደላ ብቻ እንዲወሰን አደረገዉ /ዋግሹም የሰቆጣ አካባቢ የማዕረግ ስም ነዉ/፡፡
---
👑 ተዋበች ወይስ ቴዎድሮስ?
ለዚህም ነዉ እንግዲህ እቴጌ ተዋበችን እንደ ዋና ቴዎድሮስን እንደ ተጨማሪ /አጋዥ/ ለማድረግ የምንገደደዉ፡፡ በእርግጥ የፖለቲካዉን ስራ ሙሉ በሙሉ ለእቴጌ ልቀዉት ስለነበረ እሱ ነበር አድራጊፈጣሪዉ፡፡
ነገር ግን ተዋበች ባልኖረች ጊዜ ቴዎድሮስ ንጉስ ሆኖ መቀጠል አልቻለም፤ መጀመሪያም ዝም ያሉት እሷ ስለሰጠቻቸዉ ነበር ማለት ነው፡፡
ምክንያቱም እሷ ከሞተች በኋላ ወዲያው በሚለከፉበት የማደሪያ ሙከራዎች ምክንያት ጭንቀት ውስጥ ገባ፤ ቤተመንግስቱንና መላውን ግዛቱንም አስለቀቁት።
ስለዚህ ቴዎድሮስን ያነሱት እሷ ነበሩ ማለት ነው። እናም የቴዎድሮስ መንግስት የቆመው እሷ እስካለችበት ጊዜ ድረስ ብቻ ከሆነ ዋናዋ እሷ ነበረች ማለት ነው፡፡
ልክ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ መንግስቱ የሚቆመዉ በተቀባዉ በእንጅንሊቱ ንጉስ ላይ ሳይሆን ባነሳዉ መስፍን ላይ ነበር፡፡
አሻንጉሊት ንጉሱ ኖረም አልኖረም ችግር የለዉም ነበር፤ ካስፈለገ አሻንጉሊት ንጉሱ ሊቀየር ይችላል፡፡ አሻንጉሊት ንጉሱ እንደተቀባ ንጉስ የሚኖረዉ ደግሞ ያነሳዉ መስፍን እስካለ ድረስ ብቻ ነበር፡፡
---
🔥 የእቴጌ ተዋበች ሚና
የእነ ቴዎድሮስን ጉዳይ ስናየዉ ከተዋበች አሊ ይልቅ ቴዎድሮስ ባይኖር ይሻል ነበር፡፡ ቴዎድሮስ ባይኖርም ሰራዊቱ አይበተንም ነበር፡፡ መሳፍንቶቹም ለአቴጌ ተዋበች አሊ መገዛታቸዉን ይቀጥሉ ነበር፡፡
ስለዚህ ምን ይሻላል ? አሻንጉሊቱ ማን ይሁን ?
ተዋበች ከሞት ስላኖረችና በዘመኑ የነገስታት ልጆች የእናት-የአባትን ስልጣን ለመወረስ ይሽቀዳደሙ ስለነበር ነዉ ቴዎድሮስን እዚህ ደረጃ ላይ ያደረሱት፡፡
እናም ቴዎድሮስ እቴጌ ተዋበችን ተጠግቶ ነበር ንግስና የኖረዉ ማለት ነው፡፡
/ልክ አሻንጉሊቱ ንጉስ ወራሹን መስፍን ተጠግቶ ንግስ እንደሚኖረዉ/
አሻንጉሊቱ ንጉስ ንግስ /ተቀብሎ/ የሚቆየዉ ደግሞ ያነሳዉ መስፍን እስካለ ጊዜ ድረስ ብቻ ነበር፡፡
ቴዎድሮስም ንግስ /ተቀብሎ/ የኖረዉ ተዋበች እስካለች ጊዜ ድረስ ብቻ ነው፡፡
ስለዚህ ከመስፈርቱ አንጻር መሳፍንቱን /ገዢን/ መከተል ስላለብን የቴዎድሮስን ሙሉ በሙሉ አሻንጉሊት ንጉስ ለማለት ባይቻልም የእቴጌዋ ረዳት /አጋዥ/ ለማድረግ እንገደዳለን፡፡
ለዚህም ነዉ ቴዎድሮስ ከእቴጌ መነን ሊበን አመዴ እጅ ወጥቶ አያዉቅም የሚባለዉ፡፡
⚔️ ከ150 ሺህ ወደ 10 ሺህ
እንግዲህ ከላይ እንዳየነዉ ተዋበች ከሞተች በኋላ የየጁ ጦር(የተዋበች) ጦር ነበሩ እየመሸሸ መጥቶ ከ150ሺ ወደ 10ሺ በመውረዱና ቴዎድሮስ ባለባት ስላልሆነ ሁሉም መሳፍንቶች መገበር አቁመዉ ቴዎድሮስን ቤተመንግስቱን አስለቅቀዉ ለዋግሹም ጎበዜ /በኋላ አፄ ተክለጊዮርጊስ 2ኛ/ መገዛት ጀመሩ፡፡
ቴዎድርሶም እስከ እንግሊዞች መምጣት ድረስ ወሎ መቅደላ ላይ መሸጎ ነበረ የሚኖረዉ፡፡ ግዛቱም ሁለት አውራጃዎች ማለትም ከበጌምድርና ከዋድላ ደላንታ አይበልጥም ነበር፡፡
🇬🇧 የቴዎድሮስ የእንግሊዝ ግንኙነት
ቴዎድሮስ ቀደም ብለዉ /ቤተመንግስቱን ከመልቀቃቸዉ በፊት/ የእንግሊዝ ንግስት ለነበሩት ለንግስት ቪክቶሪያ ደብዳቤ ፅፈዉ የወቅቱ ቆንሲል ዳንኤል ካመሩን መርጠዉ "...የጦር መሳሪያ እርዳታ፣ የጦር መሳሪያ የሚያመርቱ የአጅ ጥበብ ባለሙያዎች ...ወዘተ..." በማለት በዲፕሎማሲያዊ ቃላት የተጀበበ ደብዳቤ አስይዘዉ ልከዉ ነበር፡፡
ነገር ግን የላኩት ሰዉ የዉሀ ሽታሆነባቸዉ፡፡ ምላሽ ሲጡፉ በአካባቢያቸዉ ያገኙትን ምድር ቆንሲል ሌቃወመዉ 30 የሚያደርሱ የዉጭ ዜጎችን ወሎ መቅደላ አምባ በሚገኘዉ እሰር ቤታቸዉ እስረዉ የጦር መሳሪያ ለማስራት ሞከሩ፡፡ እንግሊዛዊያኑም በርከት ያሉ ነበር፡፡
---
🔥 የመጨረሻው ጥያቄ
ከተዋበች ሞት በኋላ ምንም አይነት ሰላምና ስልጣን ኖሮት የማያዉቀዉና ቤተመንግስቱንና መላዉን ግዛቱን እስኪለቅ የደረሰዉ ቴዎድሮስ፤ የተሻለ የጦር መሳሪያ አስመጥቶ፤ ካልተቻለ ደግሞ አስፎ፤ መሳፍንቱን ሁሉ በማንበርከክ ወደ ጎንደር ቤተመንግስት ለመመለስ በእጁ ያሉትን አማራጮች ሁሉ በሙሉ መሞከሩን ቀጠለ፡፡
በዲፕሎማሲ ማግኘት ያልቻሉትን የዘመናዊ መሳሪያ ጥማት፤ ሙያዉ በሌላቸዉ ሰዎች በግድ ለማግኘት "እንደምንንም መድፍ ስሩ" ብለዉ እስረኞችን አስገደደ፡፡
እንግሊዞች ደግሞ ሁሉም መረጃ /information/ ነበራቸዉ፡፡ ቴዎድሮስ አሁን መንግስት አይደለም፤ ቤተመንግስቱንና መላዉን ግዛቱን ለቆ ወሎ መቅደላ አምባ ላይ መሸጎ ነዉ የሚኖረዉ፡፡
በፊት መንግስት በነበረበት ሰአት ባለሙያ ጠይቀዉ ቢሆን ኖሮ ምናልባት ሊልኩልት ይችሉ ነበር፤ እሱ ግን በፊት ሰላም በነበረበት ሰአት ይህን መሳሪያ የማስራት ጉዳይ አስቦት አያዉቅም፤ አሁን ግን መንግስት ስላልሆነና ገና እንግሊዞችን የጦር መሳሪያ አስርቼ ወደ ቤተመንግስተ እመለሳለሁ ብሎ ተስፋ ያደረገ ሽፍታ ቡድን ነበረ።
ወሎዬን የካደ የወሎ አሽከር ነበረ።
🔥 እንግዲህ ጥያቄው እንደገና ይመለሳል፦
ቴዎድሮስ የራሱ ኃይል ያለው ንጉሥ ነበር? ወይስ የእቴጌ ተዋበች የፖለቲካ ጥላ ውስጥ የቆመ ንጉሥ?
https://mikysultan.blogspot.com
🔗 https://t.me/Oromo_geography
💬 እናንተ ምን ትላላችሁ?
★ Miky Sultan Barento ★
#አፄቴዎድሮስ #እቴጌተዋበች #ራስአሊ #የየጁ #ወሎ #መቅደላ #ዋግሹምጎበዜ #ዘመነመሳፍንት #MikySultanBarento
Sunday, September 6, 2026
የራስ አሊ ጀግንነት
🇪🇹⚔️ የየጁ የራስ አሊ ጀግንነት — የጦር ስልት
በኢትዮጵያ ጀግና ሰራዊት የየጁ ኦሮሞ ሰራዊት ነበረ።
የጎንደርና የሌሎችም አካባቢ ሴቶች በግጥም እየዘፈኑ፦
«“አሊና አሊና አሊና በሞቴ፤
የአማራ ማተብ ሰለቸዉ አንገቴ”»
እያሉ ይዜሙ ነበር።
★ Miky Sultan Barento ★
📜 ዘመነ መሳፍንት / በዘመነ የጁ /
ይህ በግልፅ የታየው በዘመነ መሳፍንት ጊዜ ነው።
ስለ ዘመነ መሳፍንት ጋዜጠኛ ፍስሐ ያዜ “የኢትዮጵያ የ5ሺ ዓመት ታሪክ፤ ከኖህ እስከ ኢህአዴግ” በሚለው መፅሀፋቸው ካሰፈሩት ውስጥ፦
«“በዚህ ዘመን አካባቢ በሙላ ሀገሪቱ እጅግ ግዙፍ ሰራዊት ያላቸው መሳፍንቶች የተፈጠሩበት ዘመን ነበር።»
«በተለይ የየጁው ትልቁ ራስ አሊ በሀገሪቱ ሁሉ ስሙ ከንግሱ በላይ እየገነነ መጣ። የየጁም፤ የጎንደርና የሌሎችም አካባቢ ሴቶች በግጥም እየዘፈኑ “አሊና አሊና አሊና በሞቴ፤ የአማራ ማተብ ሰለቸዉ አንገቴ” እያሉ ይዜሙ ነበር።”»
⚔️ የትልቁ ራስ አሊ ሰራዊት
የትልቁ ራስ አሊ ሰራዊት ወሎንና ጎንደርን ሙሉ በሙሉ እየወረረ ወደ ቤተመንግስቱ ተጠጋ።
በዚህ ጊዜ በየግዛቱ ያሉ የንግሱ መሳፍንቶች ከያሉበት ተሰብስበው ራስ አሊን ለመወጋት ተስማሙ።
በዚህም፦
• የየጁው ራስ ሀይሉ
• የሰሜኑ ራስ ገብሬ
• የላስታው ዋግ ራስ ስዩም
• የትግራዩ ደ/ች ወልደ ገብርኤል
• የቆጣው ራስ ደመ ክርስቶስ
• የአለፋ ጣቁሳው ደ/ች ዘክርስቶስ
• የቋራው መስፍን አዛዥ ልደቱ…
ወዘተ ሁሉም የንግሱ መሳፍንቶች ህብረት ፈጠሩና ጦራቸውን ይዘው ወደ በለሳ ተጉዘው፤ “መደብ” ተብላ በምትጠራው ቦታ ሰፈሩ።
⚔️ የመደብ ጦርነት
በአጠቃላይ በሙላ ሀገሪቱ ያሉት የንግሱ መኳንንት ሁሉ ተጣጥመው በምድረ “መደብ” ያገራችንን ትልቁን ዉጊያ አካሄዱ።
እስክ አሁንድረስ በገራችን ውስጥ በርካታ ከባድ ጦርነቶች ቢካሄዱም ሁሉም የዉጭ ድጋፍ ያለባቸውና አሸናፊነታቸውም በዉጭ ድጋፍ መጠንና ጥራት ላይ የተመሰረተ ነው።
በገራችን ውስጥ የዉጭ ድጋፍ የሌለበት ይህን የሚያህል ከባድ ጦርነት እስክ አሁን ድረስ ተካሂዶ አያውቅም።
የየጁዎች መሀል ሀገር ውስጥ ስለሚገኙ ምንም አይነት የዉጭ ድጋፍ ያልነበራቸውና እጅግ ኋላ ቀር መሳሪያ የታጠቁ ነበሩ።
በአንፃሩ በንግሱ በኩል ያለው ሀይል ከግራኝ ጀምሮ ሲማረክ የኖረ፤ ፓርቱጋሎች ሲመጡ ያመጡትና በየጊዜው ሲገዛ የኖረ በርካታ የዘመኑ መድፎችንና ሌሎች የተሻሉ መሳሪያዎችን የታጠቀ ነበር።
⚔️ የየጁ የጦር ስልት
ሆኖም የመንግስት ጦር የታጠቀውን መሳሪያ ለመጠቀም አስቸጋሪ ሆነበት።
ምክንያቱም የየጁዎች የሚተኩሱት ነገር ስለሌላቸው፤ የጦርነት ስልታቸው ፈጣን መቀላቀልና የጨበጣ ጦርነት መጀመር ነበር።
ስለሚቀላቀሏቸው የንግሱ ወታደሮች ወደ የትም አቅጣጫ መተኮስ አልቻሉም ነበር።
እናም የየጁው ጦር የሞተዉ እየሞተ እጅግ በፍጥነት ስለሚቀላቀል የመንግስት ተኳሾች ጠላትን ከወገን ለይተው ለመምታት ይቸገሩ ነበር።
እናም በአካባቢው ቀጥቃጮች የተሰሩ ጦርና ጎራዴ ብቻ የታጠቀው በየጁ ሰዎች የተዋቀረው /የሚመራው/ የራስ አሊ ጦር ክፍተኛ አጠቃ፤ የተጣመረዉ የንግሱ ሀይልም የሞት ሽረት መከላከል አደረገ።
ነገር ግን የየጁዉን ሰራዊት እጅግ ፈጣን ማጥቃት የሚቋቋመው አልተገኘም።
እናም የንግሱ ጦር ያለቀው አልቆና የተማረከው ተማርኮ የተረፈው ተበተነ።
ራስ ደመ ክርስቶስ በዉጊያው ላይ ሲሞት ሌሎች መኳንንቶች ወታደሮቻቸውን አስፈጅተው በየቦታው ሸሹ።
ሁሉም የሀገሪቱ መሳፍንቶች ተሰብስበው አንድ ቦታ ላይ ስለተመቱ፤ ትልቁ ራስ አሊ ያለማንም ከልካይ መላዋን ሀገሪቱንና የጎንደር ቤተመንግስትን ተቆጣጠሩ” ይላል።
📌 ይህ ጦርነት የወሎ የእርስ በእርስ ጦርነት ነበር?
በነገራችን ላይ ይህን ጦርነት የወሎ የእርስ በእርስ ጦርነት አድርጎ መውሰድ አይቻልም።
ምክንያቱም በንግሱ በኩል /በሸዋዎች በኩል/ ሌሎች የሀገሪቱ መሳፍንቶች ሁሉ አብረው ተሳተፈዋልና።
ስንደርስበት በዝርዝር እናየዋለን።
🏛️ የጎንደር ቤተመንግስት ከተቆጣጠሩ በኋላ
ትልቁ ራስ አሊ መላዋን ሀገሪቱንና የጎንደር ቤተመንግስትን ሲቆጣጠሩ ሁሉም የክርስቲያን ባላባቶች “መደብ” በሚባለው ቦታላይ ተሰብስበው አንድ ላይ ስለተመቱ በሀገሪቱ ውስጥ አንድም የክርስቲያን ሀይል አልነበረም።
ስለዚህ ያለማንም ከልካይ እስልምናን ማወጅ ይችሉ ነበር ማለት ነው።
የየጁ ሰው አብዛኛው ሙስሊም ሆኖ ሳለ ግን አስገድድ አይልም ሀይማኖቱ ብፈልግ ኖሮ ትልቁ ራስ አሊ ያለማንም ከልካይ እስልምናን አወጀው ሀገሪቱን መጨረሻዉ ለማይታወቅ ዘመን ያህል ይመሩ ነበር ማለት ነዉ።
ምክንያቱም እስልምናን አወጀው ቢሆን ኖሮ ካሳ ሀይሉ /ቴዎድሮስ/ ክርስቲያን ስለሆነ ቤተመንግስት ውስጥ ቢቀጠርም ያን ያህል ሹመት የማግኘት እድሉ ጠባብ ነበር፤ እናም አጼ ቴዎድሮስ የሚባል ንጉስ አይከሰትም ነበር ማለት ነው።
ስለዚህ የየጁዎች ግዛት ከ74 አመት በላይም ሊቀጥል ይችላል ነበር ማለት ነው።
እናም ከአጋሜዎች /ከላስታዎች/ና ከሸዋዎች በተጨማሪም ከዚህ ከዘመነ መሳፍንት ጦርነትም በድጋሜ በግልፅ እንደምንረዳው የየጁዎች አብዛኞቹ ሙስሊም ብሆኑም በሀይማኖት አለስገደዱም እንጂ ኢትዮጵያን ሙስሊም ከመሆን ማንም አላዳናትም ነበር ማለት ነው።
/ትልቁ ራስ አሊ መላዋን ሀገሪቱንና የጎንደር ቤተመንግስትን ሲቆጣጠሩ ሁሉም የክርስቲያን ባላባቶች “መደብ” በሚባለው ቦታ ላይ ተሰብስበው አንድ ላይ ስለተመቱ በሀገሪቱ ውስጥ አንድም የክርስቲያን ሀይል አልነበረም/።
https://mikysultan.blogspot.com
🔗 https://t.me/Oromo_geography
★ Miky Sultan Barento ★
የየጁ ኦሮሞ ታሪክ
🇪🇹📜 የወሎ ታሪክ — ታሪክን የኋሊት የጁ
ዘመነ መሳፍንት በሚባለው የየጁዎች መንግስት ወቅት እንዲህ ሆነ፤ ራስ አሊ የጁ የተባለ ጀግና ጎፈሬ መስፍን አገሪቱን ይመራ ነበር፤ ከእሱ በታች፤ በነ ራስ አሊ ትዛዝ ደጃች ውቤ የተባለ ባለሹርባ መስፍን፤ ከስሜን እስከ ምፅዋ ያለውን ግዛት ያስገብራል።
የሆነ ጊዜ ላይ ውቤ ደጃዝማችነቱ አላረካው አለ፤ መፈንቀለ መንግስት ማድረግ ፈለገ፤ ደጁን ብቻ ሳይሆን ሙሉውን ግቢ ፈለገው፤ ለመንገስ በጣም ሻፈደ።
በምፅዋ በኩል ብዙ ጠመንጃ እየሰበሰበ አካማቸ፤ ብዙ ጭፍራ መለመለ፤ የሚቀማውን ስልጣን የተገባ Legitimate ለማድረግ አባ ሰላማ የተባለ የግብፅ ቅጥረኛ ጳጳስ አሰናዳ፤ የሚቀረው ምንድነው? ራስ አሊን ከስልጣን ማባረር።
ታሪኩን ላሳጥረውና፤ ራስ አሊና ውቤ ደብረታቦር ላይ ገጥመው ተፈሳፈሱ!
በጦርነቱ ላይ የውቤ ባለነፍጥ ሰራዊት የራስ አሊን ፈረሰኛ እንደ ቅጠል ያረግፈው ጀመር፤ የራስ አሊ ፈረሰኛ በጎራዴ ነበረ የምዋጋ፤ የራስ ውቤ በግብፆችና በክሪስትያን ሀገሮች እገዛ የተገኛ መሳርያ ነበረ።
ነገሩ ያላማረው ራስ አሊ ብረት-ለበሱን ማለቴ ፈረሱን የኋሊት አዞረና ቆሰቆሰው፤ አብዛኞቹም ወታደሮቹም ተከትለውት ሸሹ፤ የጦርነት ስልት ነው።
ውቤ፤ ነገሩ አሸወይና እንደሆነ ሲመለከት ድንኳኑን ጥሎ አስደግሶ ወታደሮቹን የድል ምሳ ጋበዘ። ምሳው እየተበላ፣ ጠጁ እየተጠጣ፣ ወታደሮች እየመጡ ይፎክራሉ፤ ምርኮኞችም ደግሞ መሳርያቸውን እየጣሉ በውቤ ፊት ይንበረከካሉ።
በዚህ መሀል፤ የወሎው ጀግና አሊጋዝ ብሩ የተባለ እውቅ፤ የየጁ ጀግና ወደ ደጃች ውቤ ቀረበ። ሌሎች ምርኮኞች እንደሚያደርጉት መሳርያውን የሚያስቀምጥ ይመስል በርከክ እንደማለት አለና፦
“እጅ ወደላይ!”
ብሎ ጮኸ!
ውቤ ቁጭ ባለበት ደርቆ ቀረ፤ ምንም ማድረግ አልቻለም። እየጋጠ የነበረውን የዶሮ ቅልጥም ማእዱ ላይ አስቀምጦ እጁን ወደ ላይ አነሳ።
(የቅልጥሙን ቀደዳ እንኩዋን እኔ ነኝ የጨመርኩት)
ራስ አሊ፤ ከሸሸበት ቦታ ሆኖ አንድ መልክት ደረሰው፦
“ውቤ ተማርከዋልና ይመለሱ” ይላል መልእክቱ።
ላኪው አሊጋዝ ብሩ የየጁ ጀግና ነው።
ይህ በሆነ በማግስቱ አንዲት ባልቴትና እና አንድ ሰውየ መንገድ ላይ ተገናኙ።
“እቴዋ! የራስ አሊና የደጃች ውቤ ጦርነት እንዴት አለፈ?” አለ ሰውየው።
“ራስ አሊ ሸሹ፤ ደጃች ውቤ አሸንፈው ተማረኩ” አሉ ባልቴቲቱ።
“እረ ባክዎ በቅጡ በቅጡ አድርገው ያውጉኝ!”
“ተወኝ ባክህ! እነሱ በቅጡ ያልተዋጉትን እኔ እንዴት በቅጡ ላውጋው?”
---
🧠 ከዚህ አጭር የታሪክ ገጠመኝ የምንማረው የዘመናዊ ፖለቲካ ንድፈ ሀሳብ
“የሚሸሽ ሁሉ የተሸነፈ አይደለም፤ የሚያሸንፍ ሁሉም አሸናፊ አይደለም።”
ይህ የውቤ ታሪክ እንደ ተራ የጦርነት ገጠመኝ ብቻ ከተመለከትነው ብዙ ነገር እናጣለን። ነገር ግን ከፖለቲካ ስልት አንፃር ስናነበው የሚያስተምረን ነገር አለ።
ውቤ የጦር ሜዳውን አሸነፈ ብሎ አሰበ። ስለዚህ የድል ምሳ አዘጋጀ።
ራስ አሊ ግን ወደኋላ ተመለሰ። ይህ ሽንፈት ይመስል ነበር።
ነገር ግን ጨዋታው እዚያ አልተጠናቀቀም።
የውቤ ድል ወደ የድል ምሳ ሲቀየር፣ የራስ አሊ ሽንፈት ወደ የፖለቲካ ውጤት ተቀየረ።
ይህ ነው የፖለቲካ ስልት።
አንድ ኃይል በዛሬው የጦር ሜዳ ሊያሸንፍ ይችላል፤ ሌላው ደግሞ በዛሬው ጦርነት ሊሸሽ ይችላል።
ግን የመጨረሻውን ውጤት የሚወስነው የመጀመሪያው ቅጽበት አይደለም።
የሚወስነው፦
ማን እስከመጨረሻ አስቦ ነው?
ማን የተቃዋሚውን ቀጣይ እርምጃ አይቷል?
ማን በድል ስሜት አልተዘናጋም?
ማን የሕዝብን ድጋፍ ማቆየት ችሏል?
የዛሬ ኢትዮጵያ ፖለቲካም በዚህ መነፅር ሊታይ ይችላል።
የዛሬን ድል ብቻ አትመልከት፤ የነገን እርምጃ ተመልከት።
የዛሬ ሽንፈትንም የመጨረሻ ሽንፈት አድርገህ አትቁጠር።
ምክንያቱም፦ የፖለቲካ ጨዋታ እስካልተጠናቀቀ ድረስ የድል ምሳ ማዘጋጀት አደገኛ ነው።
https://mikysultan.blogspot.com
🔗 https://t.me/Oromo_geography
🔥 ታሪክን የኋሊት ስናየው፣ የዛሬን ፖለቲካ የበለጠ እንረዳለን።
— Miky Sultan Barento
Subscribe to:
Posts (Atom)
ንጉሥ ሙሀመድ አሊ
👑🔥 ንጉሥ ሙሀመድ አሊ (አባ ሻንቆ) ዘበሔረ ወሎ — የወሎ አንበሳ! 🔥👑 ★ Miky Sultan Barento ★ “ሻንቆ” የፈረስ ስማቸው ነው፤ ጀግንነትን ያሳያል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🌿 የወሎ ኦሮ...
-
ጀማሉዲን ሙሀመድ አኒ (አራርሶ ሮውብሶ) https://t.me/Oromo_geography * ــــــــــــــــــــــــــــــــــــ * ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የዒልም ኮኮብና የጅሀዱ ጀግኖ...
-
የባሬንቶ ልጆች እና የሰሜኑወሎናራያ ውልድ ዘር ሀረግ የሰበት ወሎ ጎሳ ኮንፍድሬሽን ታሪክ … ቦረና እና ባሬንቶ ኦሮሞ ትላልቅ ሁለት ልጆች ወይም ጎሳዎች አሉት፣ እነሱም። ቦረነና ባሬንቶ ...
-
®የ ወሎ የዘር ሀረግ☜ አዘጋጅ ፤miky sultan/wollo oromo.********** የካም ልጆች ኩሽ ፣ፋጥነ ከነዓን ናቸዉ፣ ከነዚህ መሃል የወሎ የዘር ሀረግ ከኩሽ ይመዘዛል ኦሮሞ የ ኩሽ ዘር ነው...









