Translate

Wednesday, September 9, 2026

ራስ ይማም የጁ

👑⚔️ ራስ ይማም የጁ — የዘመነ መሳፍንት ታላቅ መሪ ⚔️👑 ★ Miky Sultan Barento ★ 📜 ራስ ይማም የጁ (Ras Yimam of Yejju) የየጁ ኦሮሞ የወራ ሸህ ሥርወ-መንግሥት ኃይለኛ መሪ ሲሆን፣ የራስ ጉግሳ ወሌ መርሶ ባሬንቶ ልጅ ነበር። አባቱ በ1825 ከሞተ በኋላ፣ ራስ ይማም የአባቱን ሥልጣን ተረክቦ የበጌምድር መሪና እንደራሴ ሆነ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 👑 ወደ ሥልጣን ራስ ይማም ከ1825–1828 ድረስ በዘመነ መሳፍንት ውስጥ የየጁን የፖለቲካ ተፅዕኖ ለማስቀጠል ተጋድሎ አደረገ። በዚህ ወቅት የሴሜን፣ የደምቢያ፣ የጎጃምና የሌሎች ክልላዊ መሪዎች ፈተናዎች ነበሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚔️ ከሴሜን መሪዎች ጋር በዚያን ጊዜ ደጃዝማች ኃይለ ማርያም ከሴሜን ተነስቶ በጎንደር ዙሪያ የነበረውን የየጁ ተፅዕኖ ለመቃወም ሞከረ። ራስ ይማም ግን ከዘመቻው ተመልሶ ኃይለ ማርያምን ተከትሎ ወደ ወልደባ ደረሰ። በዚያም ለሦስት ቀናት ውጊያ ተካሄደ። በመጨረሻም ኃይለ ማርያም ወደ ወገራ ተመለሰ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚔️🔥 የኮሶ በር ጦርነት — 1827 🔥⚔️ ከራስ ይማም የታሪክ ጉዞ ውስጥ በጣም የሚጠቀሰው የኮሶ በር ጦርነት ነው። በ1827 ራስ ይማም ከደጃዝማች ውቤ ኃይለ ማርያም ጋር ተባብሮ፣ የደጃዝማች ጎሹ ዘውዴንና የደጃዝማች ማሩ የደምቢያን ኃይል ተዋጋ። ⚔️ የይማምና የውቤ ጥምር ኃይል ድል አደረገ። 🕯️ በዚያም ጦርነት ደጃዝማች ማሩ ሞተ። ይህ ድል ራስ ይማም በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ያለውን የየጁ የፖለቲካ ኃይል ለጊዜው እንዲጠናከር አድርጓል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚖️ የሥልጣን ፖለቲካ የዘመነ መሳፍንት ፖለቲካ በቋሚ ጥምረት ላይ የተመሠረተ አልነበረም። 👉 ዛሬ የሚተባበሩ መሪዎች፣ ነገ ሊጋጩ ይችሉ ነበር። ራስ ይማምም ከውቤ ጋር ተባብሮ ከደጃዝማች ማሩና ጎሹ ጋር ተዋጋ። ይህም የዚያን ዘመን ፈላጭ ቆራጭ የክልላዊ ሥልጣን ፖለቲካ ያሳያል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🕌 ከሃይማኖት ፖለቲካ ጋር ያለው ግንኙነት አንዳንድ ታሪካዊ ምንጮች፣ በተለይም የJ. Spencer Trimingham ጥናት፣ ራስ ይማም ለእስልምና የሚያደላ አቋም እንደነበረው ይጠቅሳሉ። ይህ ጉዳይ ግን ከዘመኑ የሃይማኖትና የፖለቲካ ግጭቶች አንፃር መታየት ይገባዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🕯️⚔️ 1828 — የራስ ይማም መጨረሻ ⚔️🕯️ ራስ ይማም በ1828 በደብረ ታቦር በግድያ ሞተ። ከዚያም የየጁ ሥልጣን ወደ ወንድሙ ራስ ማርዬ (Marye Gugsa) ተላለፈ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌 በአጭሩ፦ 👑 ራስ ይማም የጁ ➡️ የራስ ጉግሳ ወሌ መርሶ ልጅ ➡️ የየጁ ሥርወ-መንግሥት መሪ ➡️ እንደራሴ የኢትዮጵያ ➡️ 1825–1828 በሥልጣን ላይ ➡️ 1827 በኮሶ በር ጦርነት ድል ተቀዳጀ ➡️ 1828 በደብረ ታቦር ሞተ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🔥 ራስ ይማም የጁ በዘመነ መሳፍንት የየጁ ኦሮሞ የፖለቲካ ተፅዕኖ ከፍተኛ በነበረበት ዘመን የሚታወስ መሪ ነው። https://mikysultan.blogspot.com 🔗 https://t.me/Oromo_geography 👑⚔️ የየጁ ታሪክ — የኢትዮጵያ ታሪክ አንድ አካል! ⚔️👑 ★ Miky Sultan Barento ★

ራስ ማርዬ የየጁ

👑⚔️ ራስ ማርዬ የየጁ — የየጁ ኦሮሞ ታላቅ መሪ ⚔️👑 ★ Miky Sultan Barento ★ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🌳 የራስ ማርዬ የየጁ የቤተሰብ መስመር ሙሉ ስማቸው ማርዬ ጉግሳ ወሌ መርሶ ባሬንቶ ነው። 👑 ራስ ጉግሳ የየጁ ⬇️ ⚔️ ራስ ማርዬ የየጁ ⬇️ 🏛️ የየጁ ሥርወ-መንግሥት የፖለቲካ ተፅዕኖ ራስ ማርዬ የራስ ጉግሳ ልጅ ሲሆን፣ የራስ ይማም ወንድም ነበር። ከይማም በኋላ የየጁ የሥልጣን መሪነትን ያዘ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 👑 የየጁ ሥልጣንና ተፅዕኖ ራስ ማርዬ ዋና መቀመጫውን ደብረ ታቦር አድርጎ፣ በወቅቱ በኢትዮጵያ የንጉሣዊ ፖለቲካ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ያሳደረ መሪ ነበር። የየጁ ኦሮሞ ኃይልም በዚያን ዘመን በወሎ፣ የየጁ፣ በጌምድር እና በሌሎች አካባቢዎች ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ ተፅዕኖ ነበረው። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚔️🔥 ደብረ አባይ — 14 ፌብሩወሪ 1831 🔥⚔️ የራስ ማርዬ የመጨረሻው ታላቅ ዘመቻ ከደጃዝማች ሰባጋዲስ ወልዱ ጋር የነበረው ግጭት ነበር። በ14 ፌብሩወሪ 1831 ሁለቱ ኃይሎች በማይ እስላሜ፣ ደብረ አባይ አካባቢ ተገናኙ። ይህ ውጊያ የደብረ አባይ ጦርነት ወይም የማይ እስላሜ ጦርነት ተብሎም ይጠራል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🔥⚔️ የጦርነቱ ውጤት የራስ ማርዬ ወገን ድል አደረገ፤ ሰባጋዲስም ተሸነፈ። ነገር ግን ይህ ድል ከባድ ዋጋ ነበረው። 👑 ራስ ማርዬ ራሱ በዚያው ጦርነት ሕይወቱን አጣ። ሰባጋዲስም ከዚያ በኋላ ለወታደሮቹ እጅ ሰጠ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🛡️ የየጁ ኃይል ከየት መጣ? የራስ ማርዬ ዘመቻ ብቻውን የአንድ አካባቢ ጦር አልነበረም። ምንጮች ከወሎ፣ የየጁና በጌምድር የመጡ ኦሮሞ ኃይሎች፣ እንዲሁም ሌሎች አጋር ኃይሎች በዘመቻው እንደተሳተፉ ይገልጻሉ። ይህም የየጁ የፖለቲካና የወታደራዊ ተፅዕኖ ስፋትን ያሳያል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 👑⚔️ ከራስ ማርዬ በኋላ ከራስ ማርዬ ሞት በኋላ ራስ ዶሪ የየጁ ተከተለው። ዶሪም በደብረ አባይ ዘመቻ ከማርዬ ጋር አብሮ እንደመራ ምንጮች ይጠቅሳሉ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🌿📜 ታሪካዊ ትርጉሙ ራስ ማርዬ የየጁ ታሪክ ውስጥ ብቻ የሚታይ ሰው አይደለም። በዘመነ መሳፍንት የየጁ ኦሮሞ መሪዎች በኢትዮጵያ ማዕከላዊ ሥልጣን ላይ የነበራቸውን ትልቅ ሚና የሚያሳይ ታሪካዊ ሰው ነው። 🔥 በደብረ አባይ ድልን አስመዝግቦ፣ በዚያው ውጊያ ሕይወቱን የሰጠ የየጁ መሪ! ⚔️👑 https://mikysultan.blogspot.com 🔗 https://t.me/Oromo_geography ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 👑 ራስ ማርዬ የየጁ ⚔️ የየጁ ኦሮሞ መሪ 🔥 የደብረ አባይ ድል አስመዝጋቢ 🛡️ በታሪክ የተመዘገበ ስም ★ Miky Sultan Barento ★ #ራስማርዬ #የየጁኦሮሞ #ራስዶሪ #ደብረአባይ #ዘመነመሳፍንት #ወሎ #YejjuOromo #RasMarye

Ras Dori Yejju Leader

👑⚔️ ራስ ዶሪ የጁ — የየጁ ኦሮሞ ታሪካዊ መሪ ⚔️👑 ★ Miky Sultan Barento ★ 📜 ራስ ዶሪ የጁ (Ras Dori of Yejju) በዘመነ መሳፍንት መጨረሻ አካባቢ በየጁ ፖለቲካና በኢትዮጵያ የሥልጣን ትግል ውስጥ የታወቀ የየጁ መሪ ነበር። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🌿 የራስ ዶሪ የጁ የሥልጣን ዘመን ራስ ዶሪ የራስ ማርዬ የጁ ወንድም ነበር። ራስ ማርዬ በ1831 ዓ.ም. በደብረ አባይ/ማይ እስላሚ ጦርነት ከተገደለ በኋላ፣ ዶሪ የየጁን ኃይል ተረክቦ በወቅቱ የነበረውን የፖለቲካ ትግል ቀጠለ። ⚔️ ደብረ አባይ — 1831 በ1831 የተካሄደው የደብረ አባይ ጦርነት በየጁ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ያመጣ ክስተት ነበር። በዚህ ጦርነት ራስ ማርዬ ከሞተ በኋላ የየጁ የፖለቲካ አመራር ወደ ራስ ዶሪ ተሸጋገረ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 👑 ዶሪ እንደ እንደራሴ ራስ ዶሪ በወቅቱ የንጉሠ ነገሥቱ እንደራሴ (Inderase) በመሆን በንጉሣዊ ፖለቲካ ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን ያዘ። በ1831 ዓ.ም. ከነበረው የሥልጣን ትግል ጋር ተያይዞም የንጉሥ ግጋር ሥልጣን እንዲወርድ አድርጎ፣ ኢያሱ አራተኛ ንጉሠ ነገሥት እንዲሆን በማድረግ በወቅቱ የነበረውን የየጁ ተፅዕኖ አሳየ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🏹 የየጁ የሥልጣን ተከታታይ 👑 ራስ አሊ ታላቁ ⬇️ 👑 አሊጋዝ ⬇️ 👑 ራስ ጉግሳ ⬇️ 👑 ራስ ይማም ⬇️ 👑 ራስ ማርዬ ⬇️ 👑 ራስ ዶሪ ⬇️ 👑 ራስ አሊ ታናሹ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🌿 ይህ ተከታታይ የየጁ ኦሮሞ መሪዎች በ18ኛውና 19ኛው ክፍለ-ዘመን በኢትዮጵያ የንጉሣዊ ፖለቲካ ላይ ያሳዩትን ተፅዕኖ ያሳያል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚔️👑 ራስ ዶሪ የጁ — ጀግንነት፣ የጦር መሪነትና ቆራጥነት 👑⚔️ ራስ ዶሪ የጁ በ19ኛው ክፍለ-ዘመን የየጁ ኦሮሞ የፖለቲካና የጦር መሪዎች መካከል የሚጠቀስ ታሪካዊ ሰው ነው። የእርሱ የጀግንነት ታሪክ በተለይ 1831 ዓ.ም. ከተፈጠሩት የሥልጣንና የጦር ክስተቶች ጋር ይያያዛል። ⚔️ 1. በአስቸጋሪ ጊዜ አመራር መያዝ 1831 ዓ.ም. የየጁ መሪ የነበረው ራስ ማርዬ በደብረ አባይ ጦርነት ከተገደለ በኋላ፣ ራስ ዶሪ የየጁን ኃይል ተረከበ። ይህ በጣም አስቸጋሪ የፖለቲካና የጦር ወቅት ነበር። ዶሪ ግን በዚያ የተናጋ ሁኔታ ውስጥ የየጁን ኃይል ሰብስቦ አመራሩን ቀጠለ። 🛡️ 2. የየጁን ኃይል ከመበታተን መጠበቅ የመሪው ሞት ብዙ ጊዜ የጦር ኃይልን ሊያበታትን ይችላል። ዶሪ ግን ከማርዬ በኋላ የየጁን የፖለቲካ አቋም ለማስቀጠል ተንቀሳቀሰ። ይህም የእርሱን የመሪነት ቆራጥነት የሚያሳይ ነው። 👑 3. የጦር ኃይልን ከፖለቲካ ጋር ማጣመር ራስ ዶሪ ብቻውን የጦር መሪ አልነበረም፤ የየጁ የፖለቲካ ኃይልንም ይወክል ነበር። በ1831 ዓ.ም. እንደራሴ ሆኖ በንጉሣዊ ሥልጣን ጉዳይ ላይ ተሳትፎ የነበረውን አቅጣጫ ለመቆጣጠር ሞከረ። 🏹 4. የየጁን ተፅዕኖ ለማስቀጠል መታገል የዶሪ ዋና ጥንካሬ በግል የጦር ብቃት ብቻ ሳይሆን፣ የየጁን የፖለቲካ ተፅዕኖ ለማስቀጠል በመሞከሩ ውስጥ ይታያል። በዚያን ጊዜ የየጁ ኃይል በኢትዮጵያ የሥልጣን ሚዛን ውስጥ ትልቅ ቦታ ነበረው። ዶሪም ይህንን ተፅዕኖ ለማስቀጠል በአጭር ጊዜው ተጋድሎ አደረገ። 🕊️ 5. ከሞት በፊት የቀጠለው የየጁ አመራር ራስ ዶሪ በ1831 ዓ.ም. ታመመና በዚያው ዓመት ሞተ። የእርሱ የሥልጣን ዘመን አጭር ቢሆንም፣ ከራስ ማርዬ ሞት በኋላ የየጁን አመራር መቀጠሉ በታሪኩ የሚጠቀስ ነው። 🔥 ስለዚህ የራስ ዶሪ ጀግንነትን በተጋነነ የጦር ተረት ሳይሆን፣ በ1831 የተከሰተውን አስቸጋሪ የየጁ የፖለቲካና የጦር ሁኔታ ተቋቁሞ አመራሩን በመቀጠሉ መግለጽ ይቻላል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🕊️ የራስ ዶሪ መጨረሻ ራስ ዶሪ በ1831 ዓ.ም. በደብረ ታቦር ታመመና በዚያው ዓመት ሞተ። ከእሱ በኋላም ራስ አሊ ታናሹ (አሊ ሁለተኛ) የየጁን የፖለቲካ አመራር ተረከበ። 🔥👑 ራስ ዶሪ የጁ — በየጁ ታሪክ ውስጥ የ1831 የሥልጣን ሽግግርን የመራ ታሪካዊ ሰው! 👑🔥 https://mikysultan.blogspot.com 🔗 https://t.me/Oromo_geography #የየጁ_ኦሮሞ #ራስ_ዶሪ #Yejju #WolloOromo #ዘመነ_መሳፍንት #MikySultanBarento

Tuesday, September 8, 2026

ንጉሥ ሙሀመድ አሊ

👑🔥 ንጉሥ ሙሀመድ አሊ (አባ ሻንቆ) ዘበሔረ ወሎ — የወሎ አንበሳ! 🔥👑 ★ Miky Sultan Barento ★ “ሻንቆ” የፈረስ ስማቸው ነው፤ ጀግንነትን ያሳያል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🌿 የወሎ ኦሮሞ የቤት አሊ ታሪካዊ የውልድ ሐረግ 🌿 ወልዳቸው ከወሎ ኦሮሞ፣ በወረ ሒመኖ የተዋቀረው የቤት አሊ የትውልድ መስመር፦ 🌿 ባሬንቱማ ⬇️ 🌿 ወሎ — ወረ ሒመኖ ⬇️ ባቦ ጎዳና ⬇️ አሊ ⬇️ ሙሐመድ (አባ ጀቦ / ጅቦ) ⬇️ አመዴ ⬇️ ሊበን (አባ ጅሩ) ⬇️ 👑 ሙሐመድ አሊ (አባ ሻንቆ) 📜 ሙሐመድ (አባ ሻንቆ) → አሊ (አባ ቡላ) → ሊበን (አባ ጅሩ) → አመዴ (ኮላሴ) → ሙሐመድ (አባ ጀቦ/ጅቦ) → አሊ → ጎዳና → ባቦ የሚሉትን የውልድ ስሞች የሚያገናኝ ሙሉ የትውልድ መስመር ነው። 👑 ልጃቸው፦ ኢያሱ ሙሐመድ አሊ ሊበን → አመዴ → ሙሐመድ → አሊ → ጎዳና → ባቦ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 👑🔥 ንጉሥ ሚካኤል ዘበሔረ ወሎ 🔥👑 የወሎ ታሪክ ሲነሳ፣ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻና በ20ኛው መጀመሪያ ዘመን በጥልቅ የሚጠቀሱት ሰው ንጉሥ ሚካኤል ዘበሔረ ወሎ ናቸው። በልደታቸው ስም መሐመድ አሊ ይባሉ ነበር። አባታቸው አሊ አባ ቡላ የወሎ የማመዶች ቤተሰብ መሪ ነበሩ። መሐመድ አሊም የአባታቸውን የሥልጣን ውርስ ለማስመለስ ከልጅነታቸው ጀምሮ የረጅም ጊዜ ትግል አደረጉ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚔️🔥 የወረ ሒመኖ የሥልጣን ትግል 🔥⚔️ በወቅቱ የወሎ ፖለቲካ በተለያዩ የባላባት ቤተሰቦችና ገዥዎች መካከል በጣም የተወሳሰበ ነበር። መሐመድ አሊ የአባታቸው ሥልጣን ለእሳቸው እንደሚገባ በመከራከር የሥልጣን ትግል ጀመሩ። በዚህ ትግል ውስጥ አመዴ ሊበን (አባ ዋጠው) የተባሉት የወሎ ኃይለኛ መሪ ከመሐመድ አሊ ጋር ዋና ተቀናቃኝ ሆኑ። 📜 የወሎ ሕዝብ ለመሐመድ አሊ ያሳየው ድጋፍ በባህላዊ ቃል እንዲህ ተገልጿል፦ ««አሞራ ገደል ላይ አንበሳ አስሬ፤ እርሱ ቢበጥስም እኔም አብሬ!»» ይህ ቃል የወቅቱን የሕዝብ ድጋፍና የትግሉን ጥንካሬ የሚያሳይ ትውፊታዊ አገላለጽ ነው። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ በቦሩ ሜዳ በ አፄ ሚኒሊክና በ አፄ ዩሃንስ ተሸንፎ በግድ ክርስትና ተንስቶ ✝️ መሐመድ አሊ ወደ “ሚካኤል” በ1878 የቦሩ መዳ ጉባኤ ላይ መሐመድ አሊም ክርስትናን ተቀብለው “ሚካኤል” የሚል የክርስትና ስም አገኙ። ከዚያ በኋላ ራስ ሚካኤል በሚል ስም በመላው ኢትዮጵያ ታወቁ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🏛️🔥 ደሴና የወሎ አስተዳደር ሚካኤል የወሎን አስተዳደር ሲያጠናክሩ፣ ደሴ የአስተዳደር ማዕከል እንድትሆን ትልቅ ሚና አበረከቱ። ዛሬ ደሴ የወሎ ዋና ከተማ ሆና መታወቋ ከዚህ የታሪክ ሂደት ጋር በጥብቅ የተያያዘ ነው። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ⚔️🇪🇹 አድዋ — 1896 ንጉሥ ሚካኤል በ1896 የአድዋ ዘመቻ የወሎ ኃይሎችን በመምራት በኢትዮጵያ የድል ታሪክ ውስጥ ቦታ አላቸው። የወሎ ፈረሰኞችና ተዋጊዎች በአድዋ ዘመቻ ውስጥ የተሳተፉ ሲሆን፣ ይህም የወሎ ወታደራዊ ኃይል በዚያን ዘመን የነበረውን ጠንካራ ሚና ያሳያል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 👑 የኢያሱ አባት — የመነን አያት ንጉሥ ሚካኤል የልጅ ኢያሱ አባት ናቸው። የልጅ ኢያሱ ቤተሰብ ከኢትዮጵያ ንጉሣዊ ቤት ጋር በተገናኘ ጊዜ የወሎ ቤተሰብ የንጉሣዊ ቤተሰብ አካል ሆነ። ወይዘሮ ስህን የንጉሥ ሚካኤል ልጅ ሲሆኑ፣ በእሷ የዘር መስመር ንጉሥ ሚካኤል የእቴጌ መነን አያት ይሆናሉ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 🔥👑 ንጉሥ ሚካኤል ዘበሔረ ወሎ በወሎ ታሪክ ውስጥ ብቻ የሚታወሱ መሪ አልነበሩም። ከወሎ የሥልጣን ትግል፣ ከሸዋና ትግራይ የነበረው የዘመኑ ፖለቲካ፣ ከአድዋ ዘመቻ እና ከኢትዮጵያ ንጉሣዊ ቤተሰብ ታሪክ ጋር የተሳሰሩ ታላቅ ታሪካዊ ሰው ነበሩ። 🔗 https://mikysultan.blogspot.com 🔗 https://t.me/Oromo_geography 👑🔥 የወሎ ታሪክ ሲጻፍ፣ የንጉሥ ሚካኤል ስም መታለፍ የለበትም! 🔥👑 #ንጉሥ_ሚካኤል #መሐመድ_አሊ #አባ_ሻንቆ #ወሎ #ወረ_ሒመኖ #ደሴ #አድዋ #ልጅ_ኢያሱ #እቴጌ_መነን #የወሎ_ታሪክ #MikySultanBarento

“ኢትዮጵያ” የሚለው

🇪🇹🔥 “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃልም ከጎንደርና ከጎጃም ሰዎች አፍ ላይ አይወጣም 🔥🇪🇹 ★ Miky Sultan Barento ★ ልብ አንለውም እንጂ “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃልም ከጎንደርና ከጎጃም ሰዎች አፍ ላይ የተለመደ አይደለም፤ “ጎንደር፣ ጎጃም” ስለሚሉ ብቻ ኢትዮጵያ ያሉ ይመስለናል እንጂ “ኢትዮጵያ” የሚለው ቃል በግድ ነው ከአፋቸው የሚወጣው፤ ይህ እየሆነ ያለው ታዲያ በኢትዮጵያን ፈጣሪው ላይ /በሀገር ማቅናቱ ላይ/ እንደሌሉበት ስለሚያውቁ ነው።። ⚠️ ይህ ተከታሎ ጎንደርና ጎጃም ውስጥ ባህል እየሆነ የመጣ አደገኛ ነገር አለ፤ በአካባቢያቸው ማህበረሰብ ዘንድ እንደእነኚህ አይነት ነገሮችን ማሳየትን እንደ ስልጣኔና ጀግንነት የመቁጠር ባህል አለ፤ ይህ ባህል ለሀገሪቱ እጅግ ጎጂ ነው እናም ግልፅ መውጣት አለበት ነው እያልን ያለነው።። 🎵 ለምሳሌ ያህል፤ ጎጃም ውስጥ ከንዋይ ደበበ የበለጠ ጀግና የለም፤ ምክንያቱም ደግሞ ደስ በሚልና በግድ ጆሮ ውስጥ በሚገባ ዜማ “ጋምቤ ላይ ጋምቤ”፣ «“እንገዲህ ጎጃም ላይ ምን ተሰራ አትበሉ፤ ታሪክ ጠይቃችሁ በላይ በላይ በሉ”» በሚለው ዘፈኑ የበላይ ዘለቀን ታሪክ ከወሎ በመንጠቅ ነው።። ቀደም ሲልም እንደምሳሌ “የዜማ የቅኔ የቀሳውስት ሀገር” የሚለውን የንዋይን ዘፈን አይተናል፤ በዚህ ዘፈን ውስጥ የአፍሪካ ትልቅ ቅርፅ ላሊበላ አልተጠቀሰም፤ በሚገርም ሁኔታ “ፋሲለደስ አክሱም የታሪክ ምስክር” ሲል ፋሲለደስም የሸዋ ሰዎች ቅርፅ እንደሆነ ዘፈኑ አሳምሮ ያውቃል /ህዝቡ ታሪኩን እንደማያውቅና እንደተደነገበረ ስለሚያውቅ ነው ፋሲለደስን የጎንደር ቅርፅ ለማስመሰል “አክሱም ላሊበላ” በማለት ፋንታ “ፋሲለደስ አክሱም” ያለው/።። ይህ እንግዲህ ምን ያህል የወሎ /የኢትዮጵያ/ ታሪኮች ከአፋቸው እንደማይወጡና የኢትዮጵያ ታሪኮችንም በምን አይነት ስልት ወደ እነሱ እየቀየሯቸው እንደሆነ ያሳያል።። --- 🔥 ይህ በአጠቃላይ የጎንደርና ጎጃም ባህል ነው፤ ጎንደርና ጎጃም ውስጥ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ጀግና የምትባለውና የምትሞገሰው እንደዚሁ የወሎን ስም አጥፍተህ ታሪኩን ያንተ አስመስለህ ለህዝብ ያደረስክ እንደሆነ ነው።። ይህ ሁኔታ በየጊዜው የኢትዮጵያን ታሪክ እያጠፋና የአጼ ቴዎድሮስና የበላይ ዘለቀ ታሪክ ብቻ እያሰመሰለው ቀጥሏል።። ሌላውና ዋናው ጎንደርና ጎጃም የኢትዮጵያን ታሪክ ለመቀየር የሚከተሉት ስልት የወሎን ተፈጥሮ እንዳልወደዱት በማስመሰል የወሎን ስም ማደብዘዝ ነው፤ ነገር ግን እውነታው ሌላ ነው /ወሎን ጠልተው አይደለም፤ ምክንያቱም ለምሳሌ ያህል፤ የጎጃሙ ጀግና ንዋይ ለሐረር ዘፍኗል፤ የሐረርና የወሎ ህዝብ ተፈጥሮ ደግሞ አንድ አይነት ነው፤ የወሎና የጉራጌ ህዝብ ተፈጥሮም አንድ አይነት ነው።። ስለዚህ ወሎን ጠልተውት ሳይሆን ታሪኩ ግልፅ እንዳይወጣ ስለፈሩ ነው ማለት ነው። --- 📚 የኢትዮጵያ ታሪክ የማን ነው? የሆነም ደግሞ ይህ እነሱ የፈጠሩት ስልት እነሱን ብቻ የኢትዮጵያ የታሪክ ባለቤት ሊያደርጋቸው አይገባም፤ ሌሎች ከእነሱ እጅግ የተሻለ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ተሳታፊ የነበሩት ብሔረሰቦችም የኢትዮጵያ ታሪክ ባለቤት መሆን አለባቸው /ወሎ የሁሉም ብሔረሰቦች ድብልቅ ነው/።። ይህ የሚሆነው ታዲያ በታሪክ ስነፅሁፍና በታሪክ የዘፈን ስራ ውስጥ ሌሎች ብሔረሰቦችም ተሳታፊ ከሆኑና የኢትዮጵያን ትክክለኛ ታሪክ በየጊዜው ለህዝብ ማድረስ ከተቻለ ብቻ ነው።። ይህ ግን እየሆነ አይደለም፤ ይህ የማይሆንበት ዋናው ምክንያት ደግሞ አንዳንድ ብሔረሰቦች የሚያዩት የሚነገረው ቋንቋ አማርኛ መሆኑን ነው፤ ይህ እጅግ ስህተት ነው፤ ቀደም ሲል እንዳየነው አማርኛ ቋንቋ ከመምጣቱ በፊት የጎንደሬዎችም ቋንቋ ጋፋትኛ፣ ዛይኛና ቅማንትኛ ነበር።። ግዕዝ /አረብኛ/ ተናጋሪዎች ደግሞ በዙሪያችን ያሉት ሀገሮች አረብ በመሆናቸው ነው፤ /አረብ ocean ውስጥ ስለምንገኝ ነው/።። ቀደም ሲል እንዳየነው አማርኛ ቋንቋ የማንም ያልሆነ የወታደሮች ቋንቋ ነው፤ አረብኛው ከየመን መጥቶ ትግራይ ውስጥ ወደ ግዕዝነት ተቀየረ ከዚያም ላስታ /አጋው/ ውስጥ በወታደሮቹ አማካኝነት ወደ አማርኛ ተቀየረ።። ስለዚህ አረብኛ መናገራችንን ሳይሆን ታሪካችንን ነው ማየት ያለብን ማለት ነው።። አብዛኞቹ ጎንደር ላይ ያለው አጼው ቤተመንግስት የሸዋዎች መሆኑን እንኳ ስላማያውቁ የጎንደርን ቤተመንግስት በቴሌቪዥን ሲያዩ የኢትዮጵያ ታሪክ የማይመለከታቸው ስለሚመስላቸው ወደ የታሪክ ዘፈን ስራና የታሪክ መፅሐፍት ድርስ /ዝር/ አይሉም ።። ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው ነው የኢትዮጵያን ታሪክ እያበላሹት የቀጠሉት። --- 🤝 ለቀጣይ ትውልድ የምናስቀምጠው ታሪክ ምን ይሁን? እናም ሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ ይህን የጎጃምና የጎንደርን ማህበረሰብ የመሞገስ ባህል መከላከል፤ በስነፅሁፍና በዜማ የኢትዮጵያን ትክክለኛ ታሪክ በየጊዜው ለህዝብ ማድረስ አለባቸው ማለት ነው።። ለቀጣይም ትውልድ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ታሪክ አስቀምጦ ማለፍ ከሁሉም ብሔረሰቦች ይጠበቃል ማለት ነው።። 🇪🇹 ወደ ርዕሳችን ስንመለስ፦ በጣሊያን ዳግም ወረራ ጊዜ እንዳየነው እነዚህ በግንዛቤ ችግር የተፈጠሩ ቅሬታዎች ግልፅ ካልወጡ በስተቀር ውስጥ ውስጡን የሀገሪቱን ታሪክ ማጥፋት ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱንም አንድነት ችግር ውስጥ ሊከተው ይችላሉ።። ሸዋናወሎ በጎጃም ላይና በተለያዩ አካባቢዎች ላይ የፈፀሙት ድብደባ የሀገር ማቅናቱ /ማስፋፋቱ/ አካል እንጂ ቅሬታ የሚያስከትል ነገር አይደለም።። ሸዋና ወሎ አዋቂዎች እንደዛ ባያደርጉ ኖሮ ይህች የምትባል እጅግ ሰፊ በተፈጥሮ የበለፀገች ሀገር አትኖረንም ነበር ማለት ነው።። ስለዚህም ከዚህ ያረጀ አስተሳሰብ ከፈጠረው ኋላቀር አመለካከታችንና ጭፍንነታችን መውጣት ይኖርብናል ማለት ነው።። በአረጀ አስተሳሰብና ጭፍንነት ምክንያት የተፈጠረው የጎጃሞች ቅሬታ እያሰከተለው ያለው ጥፋት ያየነውን ሲመስል የወለጋዎች ቅሬታ ግን በወቅቱ የሀገሪቱ አጠቃላይ ችግር ከነበረው ከባሪያ ንግድ ጋር የተያያጠና በተጨባጭ ተፅዕኖ የማይገኝ የመንደር ወሬ ነው፤፤ ስለዚህም በተጨባጭ ተፅዕኖ በማይገኝ የመንደር ወሬዎች ላይ ተመስርቶ መፃፍም ሆነ ዘፈን መስራት አይቻልም ማለት ነው /ወሬዎች አላማቸው ይለያያል/።። ስለዚህም የወለጋ ቅሬታ ተፅዕኖ የማይገኝምና የወቅቱን ሁኔታ እንኳን ለማወቅ የመጣ እጅግ ያረጀ አስተሳሰብና ኋላቀር አመለካከት የወለደው ቅሬታ ነው /conservativeness የወለደው ቅሬታ ነው ማለት ነው/። ከዚህም በተጨማሪ ያች ቀደም ሲል ያጠናት ከጊቤ ወንዝ ጋር የተያያዘችው ቃልም በወለጋዎች ዘንድ ቅሬታ ሳይፈጥር አይቀርም። እናም ኢትዮጵያ ውስጥ ካለማንበብና ታሪክን ካለማወቅ ጋር የተያያዙ በርካታ ችግሮች አሉ ማለት ነው።። https://mikysultan.blogspot.com 🔗 https://t.me/Oromo_geography 🇪🇹📚 ታሪክ በማንም አካባቢ ብቻ የሚወሰን አይደለም፤ ምንጩ ተመርምሮ ለትውልድ መተላለፍ አለበት። #ኢትዮጵያ #ወሎ #ጎጃም #ጎንደር #ሸዋ #ወለጋ #ታሪክ #የኢትዮጵያ_ታሪክ

Monday, September 7, 2026

የእምባቦ ጦርነት

🔥⚔️ የሸዋ ወሎና የጎጃም ጦር ግጥምያ ⚔️🔥 ጎጃሞች ዘራፍ አበዙ የወሎ ሰው ዘምቶ አፉን አስያዘው 📜 የእምባቦ ጦርነት (Battle of Embabo) ★ Miky Sultan Barento 🕔 ከቀኑ 5 ሰዓት ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ የጎጃሞቹ ጦር መድፍ መተኮስ ጀመረ። የወሎ ጦረኞችም ወደ ጦርነቱ ተጠግተው ውጊያ ገጠሙ። ንጉሥ ሚኒሊክም አሽከሮቻቸውን ይዘው መሀል ለመሀል ገቡ። በዚህ ጊዜ የጎጃሙ ንጉሥ ተክለሃይማኖት መድፍ መተኮስ ጀመሩ። 💥 መድፉን ሁለት ጊዜ ተኮሱ። በሦስተኛው ግን መንኩራኩሩ ተመቶ ተሰብሮ ወደቀ። የጎጃም ጦርም የጦርነቱን ሁኔታ ባየ ጊዜ ደነገጠ። ⚔️ የወሎ ጦር ተጣጥፎ ከቦ አጨናነቀ። ከሁለት ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ፣ ንጉሥ ተክለሃይማኖት ቆስለው ተማረኩ፤ የወሎ ጦርም ይዟቸው መጣ። ጦርነቱ ግን እስከ 3 ሰዓት ድረስ ቀጠለ። የወሎ ጦር ከበቡት፤ የጎጃም ጦርም ለመሸሽም ለመማረክም የማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ገባ። በጦርነቱ ብዙ ሰዎች ከወደቁ በኋላ፣ የጎጃም ጦር ሙሉ በሙሉ እጅ ሰጠ፤ ጦርነቱም ተጠናቀቀ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📜 ከዚህ በኋላ የወሎን ስም የማጥፋት ዘመቻ መነሻው ይህ ጦርነት ነው ተብሎ በታሪክ ትውስታ ይነገራል። 🔥 የወሎ ታሪክ ይታወስ! 📜 ታሪክ አይጥፋ! ━━━━━━━━━━━━━━━━━━ #የእምባቦ_ጦርነት #የወሎ_ታሪክ #ወሎ #ጎጃም #ሸዋ #MikySultanBarento

የቴዎድሮስ ዙፋን ምስጢር

🔥👑 የቴዎድሮስ ዙፋን ምስጢር — እቴጌ ተዋበች ባትኖር ቴዎድሮስ አይነግስም ነበር? አፄ ቴውድሮ የራስ አሊ የጁ አሽከር ነበረ ተዋበች ባትኖር ቴድሮስ አይነግስም ነበረ ተዋበች ባትኖር ቴዎድሮስ አይነግስም ነበረ ራስ አሊ አሉላ (Ali II of Yejju) ⬇️ እቴጌ ተዋበች ራስ አሊ አሉላ መርሶ ባሬንቶ ⬇️ አያቷ፦ እቴጌ መነን ሊበን አመዴ በእናቷም በ አባቷም የባለባት ልጅ ነበረች። ★ Miky Sultan Barento ★ 📜 ወደ ጋዜጠኛ ፍስሐ ስንመለስ፦ “ቅድም ነገሩ ሁሉ ከቁጥጥራቸው ውጪ እየሆነ ሲመጣ ቁጣቸው ገነፈሎ አሁንም ካህናቱን እጣን ጠባሽ፤ ፊሰ ሰፊ፤ ራሱን ታጣቂ፤ ወገቡን ስባቂ... እያሉ ይዘልፏቸዉ ጀመረ፡፡ በርካቶችን ወደ ገደል አስወረወሯቸዉ፡፡ ብዙዎችንም እሳት እንዲነድዉ ወደ እሳት ጨመሯቸዉ፡፡ የቀሩትንም በጦር አስወጓቸዉ ይላል፤ ይህን ሁሉ ግፍ በካህናቱ ላይ ቢፈፅሙም የመሳፍንቱ አመፅ እንኳን ሊቆም እየባሰበት ሄደ፡፡ አፄ ቴዎድሮስም አመፁን መቋቋም ተሳናቸዉና የጎንደር ቤተመንግስትን ለመልቀቅ ተገደዱ፡፡ እቃቸዉን ጠቅልለዉ ይዘዉ ሄደዉ መቀመጫቸዉን ደብረ ታቦር አደረጉ” ይላል፡፡ --- ⚔️ የዋግሹም ጎበዜ መነሳት ከዚህ በኋላ የሀገሪቱ የፖለቲካ ቁልፍ የቆቀመዉ ዋግሹም ጎበዜ /በኋላ አፄ ተክለጊዮርጊስ 2ኛ/ እጅ ውስጥ ገባ፡፡ ቴዎደሮስ ደብረ ታቦር ሲያፈገፍግ ሁሉም የጦር መሳሪያና አሰራሮችን ይዞ ነበር፡፡ ዋግሹም ጎበዜም /በኋላ አፄ ተክለጊዮርጊስ 2ኛ/ ቴዎድሮስን ዙሪያዉን ከቦ እየተከታተለ ግዛቶቹን ሁሉ ነጥቆ በደቡብ ወሎ መቅደላ ብቻ እንዲወሰን አደረገዉ /ዋግሹም የሰቆጣ አካባቢ የማዕረግ ስም ነዉ/፡፡ --- 👑 ተዋበች ወይስ ቴዎድሮስ? ለዚህም ነዉ እንግዲህ እቴጌ ተዋበችን እንደ ዋና ቴዎድሮስን እንደ ተጨማሪ /አጋዥ/ ለማድረግ የምንገደደዉ፡፡ በእርግጥ የፖለቲካዉን ስራ ሙሉ በሙሉ ለእቴጌ ልቀዉት ስለነበረ እሱ ነበር አድራጊፈጣሪዉ፡፡ ነገር ግን ተዋበች ባልኖረች ጊዜ ቴዎድሮስ ንጉስ ሆኖ መቀጠል አልቻለም፤ መጀመሪያም ዝም ያሉት እሷ ስለሰጠቻቸዉ ነበር ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም እሷ ከሞተች በኋላ ወዲያው በሚለከፉበት የማደሪያ ሙከራዎች ምክንያት ጭንቀት ውስጥ ገባ፤ ቤተመንግስቱንና መላውን ግዛቱንም አስለቀቁት። ስለዚህ ቴዎድሮስን ያነሱት እሷ ነበሩ ማለት ነው። እናም የቴዎድሮስ መንግስት የቆመው እሷ እስካለችበት ጊዜ ድረስ ብቻ ከሆነ ዋናዋ እሷ ነበረች ማለት ነው፡፡ ልክ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ መንግስቱ የሚቆመዉ በተቀባዉ በእንጅንሊቱ ንጉስ ላይ ሳይሆን ባነሳዉ መስፍን ላይ ነበር፡፡ አሻንጉሊት ንጉሱ ኖረም አልኖረም ችግር የለዉም ነበር፤ ካስፈለገ አሻንጉሊት ንጉሱ ሊቀየር ይችላል፡፡ አሻንጉሊት ንጉሱ እንደተቀባ ንጉስ የሚኖረዉ ደግሞ ያነሳዉ መስፍን እስካለ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ --- 🔥 የእቴጌ ተዋበች ሚና የእነ ቴዎድሮስን ጉዳይ ስናየዉ ከተዋበች አሊ ይልቅ ቴዎድሮስ ባይኖር ይሻል ነበር፡፡ ቴዎድሮስ ባይኖርም ሰራዊቱ አይበተንም ነበር፡፡ መሳፍንቶቹም ለአቴጌ ተዋበች አሊ መገዛታቸዉን ይቀጥሉ ነበር፡፡ ስለዚህ ምን ይሻላል ? አሻንጉሊቱ ማን ይሁን ? ተዋበች ከሞት ስላኖረችና በዘመኑ የነገስታት ልጆች የእናት-የአባትን ስልጣን ለመወረስ ይሽቀዳደሙ ስለነበር ነዉ ቴዎድሮስን እዚህ ደረጃ ላይ ያደረሱት፡፡ እናም ቴዎድሮስ እቴጌ ተዋበችን ተጠግቶ ነበር ንግስና የኖረዉ ማለት ነው፡፡ /ልክ አሻንጉሊቱ ንጉስ ወራሹን መስፍን ተጠግቶ ንግስ እንደሚኖረዉ/ አሻንጉሊቱ ንጉስ ንግስ /ተቀብሎ/ የሚቆየዉ ደግሞ ያነሳዉ መስፍን እስካለ ጊዜ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ ቴዎድሮስም ንግስ /ተቀብሎ/ የኖረዉ ተዋበች እስካለች ጊዜ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ ከመስፈርቱ አንጻር መሳፍንቱን /ገዢን/ መከተል ስላለብን የቴዎድሮስን ሙሉ በሙሉ አሻንጉሊት ንጉስ ለማለት ባይቻልም የእቴጌዋ ረዳት /አጋዥ/ ለማድረግ እንገደዳለን፡፡ ለዚህም ነዉ ቴዎድሮስ ከእቴጌ መነን ሊበን አመዴ እጅ ወጥቶ አያዉቅም የሚባለዉ፡፡ ⚔️ ከ150 ሺህ ወደ 10 ሺህ እንግዲህ ከላይ እንዳየነዉ ተዋበች ከሞተች በኋላ የየጁ ጦር(የተዋበች) ጦር ነበሩ እየመሸሸ መጥቶ ከ150ሺ ወደ 10ሺ በመውረዱና ቴዎድሮስ ባለባት ስላልሆነ ሁሉም መሳፍንቶች መገበር አቁመዉ ቴዎድሮስን ቤተመንግስቱን አስለቅቀዉ ለዋግሹም ጎበዜ /በኋላ አፄ ተክለጊዮርጊስ 2ኛ/ መገዛት ጀመሩ፡፡ ቴዎድርሶም እስከ እንግሊዞች መምጣት ድረስ ወሎ መቅደላ ላይ መሸጎ ነበረ የሚኖረዉ፡፡ ግዛቱም ሁለት አውራጃዎች ማለትም ከበጌምድርና ከዋድላ ደላንታ አይበልጥም ነበር፡፡ 🇬🇧 የቴዎድሮስ የእንግሊዝ ግንኙነት ቴዎድሮስ ቀደም ብለዉ /ቤተመንግስቱን ከመልቀቃቸዉ በፊት/ የእንግሊዝ ንግስት ለነበሩት ለንግስት ቪክቶሪያ ደብዳቤ ፅፈዉ የወቅቱ ቆንሲል ዳንኤል ካመሩን መርጠዉ "...የጦር መሳሪያ እርዳታ፣ የጦር መሳሪያ የሚያመርቱ የአጅ ጥበብ ባለሙያዎች ...ወዘተ..." በማለት በዲፕሎማሲያዊ ቃላት የተጀበበ ደብዳቤ አስይዘዉ ልከዉ ነበር፡፡ ነገር ግን የላኩት ሰዉ የዉሀ ሽታሆነባቸዉ፡፡ ምላሽ ሲጡፉ በአካባቢያቸዉ ያገኙትን ምድር ቆንሲል ሌቃወመዉ 30 የሚያደርሱ የዉጭ ዜጎችን ወሎ መቅደላ አምባ በሚገኘዉ እሰር ቤታቸዉ እስረዉ የጦር መሳሪያ ለማስራት ሞከሩ፡፡ እንግሊዛዊያኑም በርከት ያሉ ነበር፡፡ --- 🔥 የመጨረሻው ጥያቄ ከተዋበች ሞት በኋላ ምንም አይነት ሰላምና ስልጣን ኖሮት የማያዉቀዉና ቤተመንግስቱንና መላዉን ግዛቱን እስኪለቅ የደረሰዉ ቴዎድሮስ፤ የተሻለ የጦር መሳሪያ አስመጥቶ፤ ካልተቻለ ደግሞ አስፎ፤ መሳፍንቱን ሁሉ በማንበርከክ ወደ ጎንደር ቤተመንግስት ለመመለስ በእጁ ያሉትን አማራጮች ሁሉ በሙሉ መሞከሩን ቀጠለ፡፡ በዲፕሎማሲ ማግኘት ያልቻሉትን የዘመናዊ መሳሪያ ጥማት፤ ሙያዉ በሌላቸዉ ሰዎች በግድ ለማግኘት "እንደምንንም መድፍ ስሩ" ብለዉ እስረኞችን አስገደደ፡፡ እንግሊዞች ደግሞ ሁሉም መረጃ /information/ ነበራቸዉ፡፡ ቴዎድሮስ አሁን መንግስት አይደለም፤ ቤተመንግስቱንና መላዉን ግዛቱን ለቆ ወሎ መቅደላ አምባ ላይ መሸጎ ነዉ የሚኖረዉ፡፡ በፊት መንግስት በነበረበት ሰአት ባለሙያ ጠይቀዉ ቢሆን ኖሮ ምናልባት ሊልኩልት ይችሉ ነበር፤ እሱ ግን በፊት ሰላም በነበረበት ሰአት ይህን መሳሪያ የማስራት ጉዳይ አስቦት አያዉቅም፤ አሁን ግን መንግስት ስላልሆነና ገና እንግሊዞችን የጦር መሳሪያ አስርቼ ወደ ቤተመንግስተ እመለሳለሁ ብሎ ተስፋ ያደረገ ሽፍታ ቡድን ነበረ። ወሎዬን የካደ የወሎ አሽከር ነበረ። 🔥 እንግዲህ ጥያቄው እንደገና ይመለሳል፦ ቴዎድሮስ የራሱ ኃይል ያለው ንጉሥ ነበር? ወይስ የእቴጌ ተዋበች የፖለቲካ ጥላ ውስጥ የቆመ ንጉሥ? https://mikysultan.blogspot.com 🔗 https://t.me/Oromo_geography 💬 እናንተ ምን ትላላችሁ? ★ Miky Sultan Barento ★ #አፄቴዎድሮስ #እቴጌተዋበች #ራስአሊ #የየጁ #ወሎ #መቅደላ #ዋግሹምጎበዜ #ዘመነመሳፍንት #MikySultanBarento

ራስ ይማም የጁ

👑⚔️ ራስ ይማም የጁ — የዘመነ መሳፍንት ታላቅ መሪ ⚔️👑 ★ Miky Sultan Barento ★ 📜 ራስ ይማም የጁ (Ras Yimam of Yejju) የየጁ ኦሮሞ የወራ ሸህ ሥርወ-መንግሥት ኃይለኛ መሪ ሲሆን፣ የራ...