Seenaa ilma nuuh "Ham " Abbaa afrikaa qaroomina kush & kana'an የኖህ ልጅ ታሪክ ሃም የአፍሪካ አባት የኩሽ እና ከነዓናዊ ስልጣኔ! For those who want to learn more about the history, culture, way of life, and civilization of the Cushites, visit our website.https://mikysultan.blogspot.com
Translate
Saturday, September 5, 2026
ንግስት ወርቂቱ
🌳⚔️ ዋርካው ምስክር ነው!
አጣዬ ሰዴን መከና
የወሎዋ ንግስት ወርቂቱ 7ቱ ጦረኞች እና የመንዝ 70 ጦር — በሕዝብ ትውስታ የኖረ ታሪካዊ ግጥሚያ 🇪🇹
━━━━━━━━━━━━━━
📜 ታሪክ በመጽሐፍ ብቻ አይኖርም… በሕዝብም ትውስታ ይኖራል!
━━━━━━━━━━━━━━
ከትውልድ ወደ ትውልድ የተላለፈው የአካባቢው ሕዝብ ትውስታ ዛሬም ይህን ቦታ ከአንድ የታሪክ ክስተት ጋር ያገናኘዋል።
👴🏾👵🏾 የአካባቢው ሽማግሌዎች ይናገራሉ፦ ምኒሊክ በአፄ ቴዎድሮስ ተማርኮ ወደ ጎንደር ተወስዶ ታስሮ ነበረ።
ከመቅደላ እስር ቤት ያስወጣችው የወሎዋ ወርቂት ነበረ ፣ የወሎዋ ባላባት ወ/ሮ ወርቂቱ ለአጃቢነት የሰጧቸውን 7 ወታደሮች ይዘው በዚህ ዋርካ ሰዴን(አጣዬ) ሥር መሽገው ነበር ይባላል።
⚔️ በወቅቱ የመንዝ ጦር ቁጥሩ ከፍ ያለ ስለነበር፣ የወርቂቱን ጦር በማቃለል የተነገረው ስነ-ቃል ዛሬም በሕዝብ ትውስታ ይነገራል፦
«“አንተን አድብኜህ፣
አንተን አጭሼህ፣ ሥላሴ ያውቃል፤
አይጥ ከድመት
መች ተረፎ ያውቃል?”»
🔥 ለዚህም የወርቂቱ ወታደሮች የሰጡት አጸፋ በሕዝብ ስነ-ቃል እንዲህ ይታወሳል፦
«🌳 “ዋርካ ድንኳኑ፣
ሸማ ገበታው፤
የማታ ማታ፣
እኛ ነን ጌታው!”»
🏆 ከዚያ በኋላ የወርቂቱ 7ቱ ወታደሮች 70ውን የመንዝ ጦር ድል እንዳደረጉ የአካባቢው ሕዝብ ይናገራል።
🗣️ የዚህን ድል ትውስታ ለማስቀመጥም ሕዝቡ እንዲህ በማለት አዚሟል ይባላል፦
«“አረ እናንተ ሰዎች፣
ሆዳችሁ አይባባ፤
ይዋጋ የለም ወይ
ሰባት እና ሰባ?”»
🌿 ዛሬ ይህ ቦታ የገበያ ስፍራ ሆኖ ቢያገለግልም፣ ለአካባቢው ሕዝብ ግን ከዚያ በላይ ነው።
ዋርካው የተፈጥሮ ዛፍ ብቻ አይደለም፤ የአያቶች ትውስታ፣ የሽማግሌዎች አስተምህሮ፣ የስነ-ቃል ቅርስ እና የአካባቢው ታሪክ ምልክት ነው። 🌳
https://mikysultan.blogspot.com
🔗 https://t.me/Oromo_geography
📜 የተነገረ ታሪክ ሲጠበቅ፣ ትውስታ ይኖራል።
ትውስታ ሲኖር፣ ታሪክ አይጠፋም።
🇪🇹 የሕዝብ ትውስታ — የትውልድ ውርስ!
★ Miky Sultan Barento ★
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
የራስ አሊ ጀግንነት
🇪🇹⚔️ የየጁ የራስ አሊ ጀግንነት — የጦር ስልት በኢትዮጵያ ጀግና ሰራዊት የየጁ ኦሮሞ ሰራዊት ነበረ። የጎንደርና የሌሎችም አካባቢ ሴቶች በግጥም እየዘፈኑ፦ «“አሊና አሊና አሊና በሞቴ፤ የአማራ ማተብ ሰለቸዉ አን...
-
ጀማሉዲን ሙሀመድ አኒ (አራርሶ ሮውብሶ) https://t.me/Oromo_geography * ــــــــــــــــــــــــــــــــــــ * ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የዒልም ኮኮብና የጅሀዱ ጀግኖ...
-
የባሬንቶ ልጆች እና የሰሜኑወሎናራያ ውልድ ዘር ሀረግ የሰበት ወሎ ጎሳ ኮንፍድሬሽን ታሪክ … ቦረና እና ባሬንቶ ኦሮሞ ትላልቅ ሁለት ልጆች ወይም ጎሳዎች አሉት፣ እነሱም። ቦረነና ባሬንቶ ...
-
®የ ወሎ የዘር ሀረግ☜ አዘጋጅ ፤miky sultan/wollo oromo.********** የካም ልጆች ኩሽ ፣ፋጥነ ከነዓን ናቸዉ፣ ከነዚህ መሃል የወሎ የዘር ሀረግ ከኩሽ ይመዘዛል ኦሮሞ የ ኩሽ ዘር ነው...

No comments:
Post a Comment