Seenaa ilma nuuh "Ham " Abbaa afrikaa qaroomina kush & kana'an የኖህ ልጅ ታሪክ ሃም የአፍሪካ አባት የኩሽ እና ከነዓናዊ ስልጣኔ! For those who want to learn more about the history, culture, way of life, and civilization of the Cushites, visit our website.https://mikysultan.blogspot.com
Translate
Sunday, September 6, 2026
የራስ አሊ ጀግንነት
🇪🇹⚔️ የየጁ የራስ አሊ ጀግንነት — የጦር ስልት
በኢትዮጵያ ጀግና ሰራዊት የየጁ ኦሮሞ ሰራዊት ነበረ።
የጎንደርና የሌሎችም አካባቢ ሴቶች በግጥም እየዘፈኑ፦
«“አሊና አሊና አሊና በሞቴ፤
የአማራ ማተብ ሰለቸዉ አንገቴ”»
እያሉ ይዜሙ ነበር።
★ Miky Sultan Barento ★
📜 ዘመነ መሳፍንት / በዘመነ የጁ /
ይህ በግልፅ የታየው በዘመነ መሳፍንት ጊዜ ነው።
ስለ ዘመነ መሳፍንት ጋዜጠኛ ፍስሐ ያዜ “የኢትዮጵያ የ5ሺ ዓመት ታሪክ፤ ከኖህ እስከ ኢህአዴግ” በሚለው መፅሀፋቸው ካሰፈሩት ውስጥ፦
«“በዚህ ዘመን አካባቢ በሙላ ሀገሪቱ እጅግ ግዙፍ ሰራዊት ያላቸው መሳፍንቶች የተፈጠሩበት ዘመን ነበር።»
«በተለይ የየጁው ትልቁ ራስ አሊ በሀገሪቱ ሁሉ ስሙ ከንግሱ በላይ እየገነነ መጣ። የየጁም፤ የጎንደርና የሌሎችም አካባቢ ሴቶች በግጥም እየዘፈኑ “አሊና አሊና አሊና በሞቴ፤ የአማራ ማተብ ሰለቸዉ አንገቴ” እያሉ ይዜሙ ነበር።”»
⚔️ የትልቁ ራስ አሊ ሰራዊት
የትልቁ ራስ አሊ ሰራዊት ወሎንና ጎንደርን ሙሉ በሙሉ እየወረረ ወደ ቤተመንግስቱ ተጠጋ።
በዚህ ጊዜ በየግዛቱ ያሉ የንግሱ መሳፍንቶች ከያሉበት ተሰብስበው ራስ አሊን ለመወጋት ተስማሙ።
በዚህም፦
• የየጁው ራስ ሀይሉ
• የሰሜኑ ራስ ገብሬ
• የላስታው ዋግ ራስ ስዩም
• የትግራዩ ደ/ች ወልደ ገብርኤል
• የቆጣው ራስ ደመ ክርስቶስ
• የአለፋ ጣቁሳው ደ/ች ዘክርስቶስ
• የቋራው መስፍን አዛዥ ልደቱ…
ወዘተ ሁሉም የንግሱ መሳፍንቶች ህብረት ፈጠሩና ጦራቸውን ይዘው ወደ በለሳ ተጉዘው፤ “መደብ” ተብላ በምትጠራው ቦታ ሰፈሩ።
⚔️ የመደብ ጦርነት
በአጠቃላይ በሙላ ሀገሪቱ ያሉት የንግሱ መኳንንት ሁሉ ተጣጥመው በምድረ “መደብ” ያገራችንን ትልቁን ዉጊያ አካሄዱ።
እስክ አሁንድረስ በገራችን ውስጥ በርካታ ከባድ ጦርነቶች ቢካሄዱም ሁሉም የዉጭ ድጋፍ ያለባቸውና አሸናፊነታቸውም በዉጭ ድጋፍ መጠንና ጥራት ላይ የተመሰረተ ነው።
በገራችን ውስጥ የዉጭ ድጋፍ የሌለበት ይህን የሚያህል ከባድ ጦርነት እስክ አሁን ድረስ ተካሂዶ አያውቅም።
የየጁዎች መሀል ሀገር ውስጥ ስለሚገኙ ምንም አይነት የዉጭ ድጋፍ ያልነበራቸውና እጅግ ኋላ ቀር መሳሪያ የታጠቁ ነበሩ።
በአንፃሩ በንግሱ በኩል ያለው ሀይል ከግራኝ ጀምሮ ሲማረክ የኖረ፤ ፓርቱጋሎች ሲመጡ ያመጡትና በየጊዜው ሲገዛ የኖረ በርካታ የዘመኑ መድፎችንና ሌሎች የተሻሉ መሳሪያዎችን የታጠቀ ነበር።
⚔️ የየጁ የጦር ስልት
ሆኖም የመንግስት ጦር የታጠቀውን መሳሪያ ለመጠቀም አስቸጋሪ ሆነበት።
ምክንያቱም የየጁዎች የሚተኩሱት ነገር ስለሌላቸው፤ የጦርነት ስልታቸው ፈጣን መቀላቀልና የጨበጣ ጦርነት መጀመር ነበር።
ስለሚቀላቀሏቸው የንግሱ ወታደሮች ወደ የትም አቅጣጫ መተኮስ አልቻሉም ነበር።
እናም የየጁው ጦር የሞተዉ እየሞተ እጅግ በፍጥነት ስለሚቀላቀል የመንግስት ተኳሾች ጠላትን ከወገን ለይተው ለመምታት ይቸገሩ ነበር።
እናም በአካባቢው ቀጥቃጮች የተሰሩ ጦርና ጎራዴ ብቻ የታጠቀው በየጁ ሰዎች የተዋቀረው /የሚመራው/ የራስ አሊ ጦር ክፍተኛ አጠቃ፤ የተጣመረዉ የንግሱ ሀይልም የሞት ሽረት መከላከል አደረገ።
ነገር ግን የየጁዉን ሰራዊት እጅግ ፈጣን ማጥቃት የሚቋቋመው አልተገኘም።
እናም የንግሱ ጦር ያለቀው አልቆና የተማረከው ተማርኮ የተረፈው ተበተነ።
ራስ ደመ ክርስቶስ በዉጊያው ላይ ሲሞት ሌሎች መኳንንቶች ወታደሮቻቸውን አስፈጅተው በየቦታው ሸሹ።
ሁሉም የሀገሪቱ መሳፍንቶች ተሰብስበው አንድ ቦታ ላይ ስለተመቱ፤ ትልቁ ራስ አሊ ያለማንም ከልካይ መላዋን ሀገሪቱንና የጎንደር ቤተመንግስትን ተቆጣጠሩ” ይላል።
📌 ይህ ጦርነት የወሎ የእርስ በእርስ ጦርነት ነበር?
በነገራችን ላይ ይህን ጦርነት የወሎ የእርስ በእርስ ጦርነት አድርጎ መውሰድ አይቻልም።
ምክንያቱም በንግሱ በኩል /በሸዋዎች በኩል/ ሌሎች የሀገሪቱ መሳፍንቶች ሁሉ አብረው ተሳተፈዋልና።
ስንደርስበት በዝርዝር እናየዋለን።
🏛️ የጎንደር ቤተመንግስት ከተቆጣጠሩ በኋላ
ትልቁ ራስ አሊ መላዋን ሀገሪቱንና የጎንደር ቤተመንግስትን ሲቆጣጠሩ ሁሉም የክርስቲያን ባላባቶች “መደብ” በሚባለው ቦታላይ ተሰብስበው አንድ ላይ ስለተመቱ በሀገሪቱ ውስጥ አንድም የክርስቲያን ሀይል አልነበረም።
ስለዚህ ያለማንም ከልካይ እስልምናን ማወጅ ይችሉ ነበር ማለት ነው።
የየጁ ሰው አብዛኛው ሙስሊም ሆኖ ሳለ ግን አስገድድ አይልም ሀይማኖቱ ብፈልግ ኖሮ ትልቁ ራስ አሊ ያለማንም ከልካይ እስልምናን አወጀው ሀገሪቱን መጨረሻዉ ለማይታወቅ ዘመን ያህል ይመሩ ነበር ማለት ነዉ።
ምክንያቱም እስልምናን አወጀው ቢሆን ኖሮ ካሳ ሀይሉ /ቴዎድሮስ/ ክርስቲያን ስለሆነ ቤተመንግስት ውስጥ ቢቀጠርም ያን ያህል ሹመት የማግኘት እድሉ ጠባብ ነበር፤ እናም አጼ ቴዎድሮስ የሚባል ንጉስ አይከሰትም ነበር ማለት ነው።
ስለዚህ የየጁዎች ግዛት ከ74 አመት በላይም ሊቀጥል ይችላል ነበር ማለት ነው።
እናም ከአጋሜዎች /ከላስታዎች/ና ከሸዋዎች በተጨማሪም ከዚህ ከዘመነ መሳፍንት ጦርነትም በድጋሜ በግልፅ እንደምንረዳው የየጁዎች አብዛኞቹ ሙስሊም ብሆኑም በሀይማኖት አለስገደዱም እንጂ ኢትዮጵያን ሙስሊም ከመሆን ማንም አላዳናትም ነበር ማለት ነው።
/ትልቁ ራስ አሊ መላዋን ሀገሪቱንና የጎንደር ቤተመንግስትን ሲቆጣጠሩ ሁሉም የክርስቲያን ባላባቶች “መደብ” በሚባለው ቦታ ላይ ተሰብስበው አንድ ላይ ስለተመቱ በሀገሪቱ ውስጥ አንድም የክርስቲያን ሀይል አልነበረም/።
https://mikysultan.blogspot.com
🔗 https://t.me/Oromo_geography
★ Miky Sultan Barento ★
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
የእምባቦ ጦርነት
🔥⚔️ የሸዋ ወሎና የጎጃም ጦር ግጥምያ ⚔️🔥 ጎጃሞች ዘራፍ አበዙ የወሎ ሰው ዘምቶ አፉን አስያዘው 📜 የእምባቦ ጦርነት (Battle of Embabo) ★ Miky Sultan Barento 🕔 ከቀኑ 5 ሰዓት ━━━━...
-
ጀማሉዲን ሙሀመድ አኒ (አራርሶ ሮውብሶ) https://t.me/Oromo_geography * ــــــــــــــــــــــــــــــــــــ * ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የዒልም ኮኮብና የጅሀዱ ጀግኖ...
-
የባሬንቶ ልጆች እና የሰሜኑወሎናራያ ውልድ ዘር ሀረግ የሰበት ወሎ ጎሳ ኮንፍድሬሽን ታሪክ … ቦረና እና ባሬንቶ ኦሮሞ ትላልቅ ሁለት ልጆች ወይም ጎሳዎች አሉት፣ እነሱም። ቦረነና ባሬንቶ ...
-
®የ ወሎ የዘር ሀረግ☜ አዘጋጅ ፤miky sultan/wollo oromo.********** የካም ልጆች ኩሽ ፣ፋጥነ ከነዓን ናቸዉ፣ ከነዚህ መሃል የወሎ የዘር ሀረግ ከኩሽ ይመዘዛል ኦሮሞ የ ኩሽ ዘር ነው...


No comments:
Post a Comment