Translate

Wednesday, January 4, 2023

#ልጅ እያሱ እና ደጃች ተፈሪ መኮንን-

ልጅ እያሱ እና ደጃች ተፈሪ መኮንን
------
(አፈንዲ ሙተቂ)
---------
ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ከበርካታ ሙስሊም ባላባቶች ጋር የተነሳቸው ፎቶግራፎች አሉ፡፡ ለምሳሌ ሀረር ውስጥ ገራድ አብዱላሂ አሊ ሳዲቅ ከሚባል የሀረር ገዥ ቤተሰብ ጋር የተነሳው ፎቶግራፍ በብዙ ስፍራዎች ተለጥፎ አይቼዋለሁ፡፡ አንዳንድ ምንጮች ያ ፎቶግራፍ ልጅ እያሱን ለመወንጀል “montage” በሚባለው የፈጠራ ጥበብ የተሰራ ነው የሚል ታሪክ ያስነብባሉ። ለምሳሌ “የሃያኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ” የተሰኘው መጽሐፍ ደራሲ “ፎቶውን የሰራው ዝነኛው እንግሊዛዊ ወታደር ቶማስ ለውሬንስ (በዓለም ታሪክ መጻሕፍት Lawerence of Arabia በሚል ቅጽል ስም የሚታወቅ) ነው” በማለት ጽፈዋል።

ሆኖም የልጅ እያሱ የልጅ ልጅ የሆኑት ፕሮፌሰር ግርማ ዮሐንስ እያሱ እንደዚህ ዓይነት ፎቶዎች እርግጠኛ ሊሆኑ እንደሚችሉ ከአስር ዓመታት በፊት “ጎህ” ለተሰኘ መጽሔት በሰጡት ቃለ-ምልልስ ገልጸዋል። ፕሮፌሰር ግርማ ስለዚህ ጉዳይ ሲናገሩ እንዲህ ነበር ያሉት።

“ከሼኮችና ከሌሎችም ጋር የተነሱአቸው ፎቶግራፎች ብዙዎች አሉ። ስለዚህ ከቄስ ጋር መነሳትም የተለመደ ነበርና ልጅ እያሱ ሁለቱንም እኩል አድርጎ ለማየት የነበራቸው ፖሊሲ አካል ነው”። (ጎህ መጽሔት፣ ቅጽ 1፣ ቁጥር 5፣ ጥቅምት 1993፣ ገጽ 13)

በቅርብ ጊዜ ስለልጅ እያሱና የአፋሮች ግንኙነት የጻፉት አራሚስ ሁመድ ሱሌ (Aramis Houmed Soulé) የተባሉ ምሁር ልጅ እያሱ ከአፋር ባላባቶችም ጋር እኝህን መሰል ፎቶግራፎች መነሳቱን አረጋግጠዋል። ስለዚህ ፎቶው “ፎርጅድ” አልነበረም ማለት ነው። ሁለቱ ምሁራን (ፕሮፌሰር ግርማ እና አራሚስ ሁመድ ሱሌ) በትክክል እንደገለጹት ልጅ እያሱ ፎቶግራፉን የተነሳበት ዓላማ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ከክርስቲያን ወገኖቻቸው ጋር እኩል መሆናቸውን ለማሳየት በሚል ነው። ታዲያ ልጅ እያሱ በመናፍቅነት በተከሰሰበት ወቅት እንዲህ ዓይነት ፎቶዎች እየተለቀሙ እንደማስረጃ ቀርበውበት ነበር።

ይህ የልጅ እያሱ መስለም በዘመኑ ብዙ የተባለለት ቢሆንም እስከ አሁን ድረስ ከአፍ ታሪክ የበለጠ ማስረጃ ሊቀርብለት አልቻለም። የእርሱ የስልጣን ባለጋራ የሆኑት ራስ ተፈሪ መኮንን (አጼ ኃይለ ሥላሴ) በጻፉት “ህይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ” የተሰኘው ግለ-ታሪካቸው ውስጥ የእያሱ ወንጀሎች በማለት ከዘረዘሯቸው አስራ አንድ ነጥቦች መካከል አስሩ አቀራረባቸው ቢለያይም ይዘታቸው አንድ ነው። ይኸውም የልጅ እያሱ መስለም ነው። እነዚህ ነጥቦች የልጅ እያሱን አራት ሴቶች ማግባት፣ መስጊድ ገብቶ መስገድና ቁርአን ማንበብ፣ መስጊድ ማሰራት፣ በኢትዮጵያ ባንዲራ ላይ “ላኢላሃ ኢለላህ” የሚል ጽሁፍ ማስጠለፍ ወዘተ… የመሳሰሉት ናቸው።

ይሁንና የልጅ እያሱ የልጅ ልጅ የሆኑት ፕሮፌሰር ግርማ ዮሐንስ “እነዚህ ሁሉ የፈጠራ ክሶች ናቸው” ነው የሚሉት። በተለይ ከተፈሪ መኮንን ጋር ከተዋጉ በኋላ ተሸንፈው በሸሹበት የአፋር በረሃ ያስጠለሏቸው የዘመኑ የአፋር ሱልጣን አቡበከር የወንድም ልጅ የሆኑት ሀንፍሬ አሊሚራህ ስለልጅ እያሱ ፍጹም ክርስቲያን መሆን ምስክርነታቸውን እንደሰጡአቸው ይገልጻሉ። አራሚስ ሁመድ ሱሌ የተባሉት ምሁርም የፕሮፌሰር ግርማን አባባል የሚያጠናክር ምስክርነት ሰጥተዋል። እኝህ ምሁር እንደጻፉት ክርስቲያኑ ልጅ እያሱ በአፋር ምድር ሳለ በክርስትና እምነቱ ከመጽናቱም በላይ አገልጋዮቹ የሰሩለትን የማሽላ ጠላ ይጠጣ ነበር። ስለዚህ ልጅ እያሱ ሙስሊሙን ከክርስቲያኑ ጋር እኩል ለማድረግ ጥረት ከማድረጉ ውጪ ለራሱ ክርስቲያን ሆኖ ነው የኖረው ማለት ነው።

ሆነም ቀረ ግን የእያሱ መስለም እርሱን ከስልጣን ለማውረድ የተደረገው ትግል ማጠንጠኛ ሆኖ ነው ያረፈው። ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ክሱ በዚህ ስልት የተቀናበረው እያሱን በህዝቡና በጦር ሀይሉ ዘንድ ለማስጠላት አመቺ መሳሪያ ሆኖ በመገኘቱ ነው ይላሉ። እንደ ፕሮፌሰሩ ገለጻ ልጅ እያሱ ቀጨኔ መድኃኒዓለምን የመሳሰሉ ደብሮችን እንዳልተከለ ሁሉ ከፍ ብሎ የሚወራው መስጊዶችን ማሰራቱ ነው። ለክሱ ማስረጃ አምጡ በሚባልበት ጊዜ “ድሮውንስ ከሙሐመድ ዓሊ ልጅ ምን ይጠበቅ ኖሯል?!” የሚል ቃለ አጋኖ ይደሰኮር ነበር። “ይሁንና” ይላሉ ፕሮፌሰር ባህሩ “ለሸዋ መኳንንት የእያሱ አደገኛነት የፖለቲካ የበላይነታቸውን ከመፈታተኑ ላይ ነበር። ስለዚህ የመናፍቅነቱ ክስ የመነጨው ለሃይማኖት ከመጨነቅ ሳይሆን ለተፈጠረው የፖለቲካ ስጋት ርዕዮተ ዓለማዊ ሽፋን ሆኖ ለማገልገል ካለው አመቺነት ነው።” (ባህሩ ዘውዴ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847-1983፡ ገጽ 134-135)

በልጅ እያሱ ላይ የሚደረገው ዱለታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰው ልጅ እያሱ አባቱን “ንጉሥ ሚካኤል” በማለት በወሎና በትግሬ ላይ ባነገሠበት ጊዜ ነው። የሸዋ መኳንንት ራስ ሚካኤል ሰሜን ኢትዮጵያን በቀጥታ ሌላኛውን የኢትዮጵያ ክልል በልጁ በኩል መቆጣጠሩን አሰመሩበት። በመሆኑም የሸዋ መኳንንት “ይህ ወጣት ከቤተ መንግሥቱ ጠራርጎ ሳያስወጣን እንቅደመው” በማለት መሯሯጥ ጀመሩ። የዚህ አድማ ዋነኛ መሪና አቀናባሪ የጦር ሚኒስትሩ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ ስለመሆኑ ምሁራን የሚስማሙበት ሐቅ ነው። 
***** ***** *****
ከዚህ በፊት እንዳጫወትኳችሁ ልጅ እያሱ የዕድሜ ልክ ባላንጣው ሊሆን የበቃውን ደጃች ተፈሪ መኮንንን በጋብቻ ጠልፎ ዝም ሊያሰኘው ሞክሮ ነበር። ይሁንና ተፈሪ የእያሱ እህት ልጅ የሆነችውን ወ/ሮ መነን አስፋውን ቢያገባም ሁለቱ ወጣቶች ፍጹም ሊጣጣሙ አልቻሉም። ተፈሪ የዘመኑ ሀብታም ክፍለ ሀገር የነበረው ሀረርጌ የዕድሜ ልክ ግዛቴ ነው ብሎ ያስብ ነበር። እያሱ ደግሞ ተፈሪ በሀረር ሀብት መበልጸጉን አልወደደውም። በተለይም ደጃች ተፈሪ ከባቡር መስመር መዘርጋት ጋር በአጭር ጊዜ ውስጥ የሀገሪቱ መንግሥት ግምጃ ቤት አለኝታ ሊሆን የበቃውን የድሬዳዋ ጉምሩክ ገቢ በቀጥታ ሊቆጣጠረው መቻሉ ለልጅ እያሱ አልተዋጠለትም።

ነገር ግን ከዚህ ክስተት በላይ እያሱን በተፈሪ ላይ ያነሳሳው የልጅ እያሱን ስም የሚያጠፋ ሚስጢራዊ ደብዳቤ ለእንግሊዝ መንግሥት ተጽፎ መገኘቱ ነው። ይህንን ደብዳቤ የጻፉት የደጃች ተፈሪ መኮንን ጸሓፊና አንድ ማንነቱ በውል ያልተገለጸ ሌላ ሰው ናቸው። ደብዳቤው በማን ትዕዛዝ እንደተጻፈ ግን የታሪክ ሰነዶች በይፋ የሚገልጹት ነገር የለም። ልጅ እያሱ “ትዕዛዙን ያስተላለፈው ተፈሪ መኮንን ነው” ባይ ነው። በዚህም ወደ አዲስ አበባ አስጠርቶት ስለጉዳዩ ቢጠይቀው ደጃች ተፈሪ ከነገሩ ንጹህ መሆኑን በመሀላ ገለጸለት። ቢሆንም እያሱ አላመነውም። በመሆኑም በሁለቱ መካከል የነበረው ቅራኔ በጣም ተባባሰ።

ነገሮች በዚህ ላይ እንዳሉ ልጅ እያሱ ተፈሪ መኮንንን ወደ አዲስ አበባ አስጠርቶት እርሱን ሳያነጋግር ወደ ሀረር ወረደ። ከሀገሬው ህዝብ ጋር ከተማከረ በኋላም ደጃች ተፈሪ መኮንንን ከሀረር ገዥነቱ ሻረው። በምትኩም የከፋ ገዥ አድርጎ ሾመውና በአስቸኳይ ወደ ተሾመበት ክልል እንዲሄድ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጠው። የድሬ ዳዋ ጉምሩክንም ወዳጁ በነበረው ሶሪያዊው ሀሲብ ይዲልቢ ስር እንዲሆን አደረገው።

የልጅ እያሱ እርምጃ ተፈሪን በጣም አስደነገጠው። “ይህ መስፍን ሊውጠኝ እያመቻቸኝ ነው” በማለት እንዲያስብም አደረገው። ስለዚህ ደጃች ተፈሪ ወደ ከፋ መሄዱን ተወና አዲስ አበባ ሆኖ የሚበጀውን መንገድ ማፈላለግ ጀመረ። ልጅ እያሱ በትዕዛዝ ላይ ትዕዛዝ ቢያዥጎደጉድለትም ደጃች ተፈሪ ልዩ ልዩ ሰበቦችን እያመካኘ በዋና ከተማይቱ ሰነበተ። የእያሱንም ልብ ለማቀዝቀዝ የስጋ ዘመዱ የሆነውን ቀኛዝማች እምሩ ኃይለ ሥላሴን (የኋለኛው ራስ እምሩ) የቃልና የጽሑፍ መልዕክት አስጨብጦ ልጅ እያሱ ወደሚገኝበት ድሬዳዋ ላከው። እያሱም የተፈሪን መልዕክት ከሰማ በኋላ እንዲህ አለ።

“ደጃች ተፈሪ አሳቡ ሁሉ ሌላ ነው። ያንዳንድ ወስላቶች ነገር እየሰማ ወዲያ ወዲህ ቢል ብርቱ ነገር ያገኘዋል። የአዲስ አበባ ወስላታ ሁሉ ፍሬ ያለው መስሎታል።” (ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣ “ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ”፣ በኢትኦጵ መጽሔት የቀረበ ጽሁፍ፣ ጥቅምት 1993፣ ገጽ 37)

ይህ የልጅ እያሱ አነጋገር በሁለቱ ልዑላን መካከል የነበረው ውጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ያመላክታል። የእያሱ ንግግር ለደጃች ተፈሪ ጆሮ ከደረሰው በኋላ ተፈሪ በስውር ማድባቱን ትቶ እያሱን ከስልጣን ለመፈንገል የሚዶልቱትን መኳንንት በይፋ ተቀላቀለ። በአስገራሚ ፍጥነትም የዱለታውን መሪነት ከፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ እጅ ወሰደው።
***** ***** *****
የሁለቱ ወጣቶች መገፋፋት ይፋ ሆኗል። ቀጣዩ ነገር “ማን ቀድሞ አጥቅቶ የአሸናፊነቱን ዘውድ ይቀዳጃል” የሚለው ብቻ ነበር። የሸዋና የምዕራብ ኢትዮጵያ ባላባቶች በተፈሪ ዙሪያ ተሰልፈዋል። የወሎ፣ የአፋር፣ የኦጋዴንና የሀረርጌ ባላባቶች የእያሱን ጎራ ተቀላቅለዋል። ቢሆንም ሁለቱ ጎራዎች በራሳቸው ወኔ ፍልሚያውን መጀመር አልቻሉም። የመጨረሻውን ፍልሚያ ለማስጀመር ሌላ ስውር እጅ አስፈልጓል። የዘመኑ ታላላቅ ቅኝ ገዥዎች እጅ!

እንግሊዝ፣ ኢጣሊያና ፈረንሳይ ሁለቱ ልዑላን ሲጣሉ መጀመሪያ ላይ አይተው እንዳላዩ ሆነው ስራቸውን ማከናወኑን ነበር የመረጡት። ከቆይታ በኋላ ግን የልጅ እያሱ የእኩልነት ፖሊሲ (በሁሉም ኢትዮጵያዊያን መካከል እኩልነትን ለማስፈን በሚል የሚወስዳቸው እርምጃዎች) የነርሱን ጥቅም የሚጎዳ መሆኑን ተገነዘቡ። የጠረፍ አካባቢ ገዥዎች ከቅኝ ገዥዎች ጋር ለሚያደርጉት ውጊያ የሞራል ድጋፍ የሚሰጥ መሆኑ አስቀየማቸው። በተለይ እንግሊዝ ሶማሌላንድን ከብሪታኒያ አገዛዝ ነጻ ለማውጣት ለ30 ዓመታት ሲዋጋ ለኖረው ሰይድ አብዱሌ ሐሰን የተሰኘ የኦጋዴን ሶማሊዎች ብሔራዊ ጀግና የመሳሪያ ድጋፍ በገፍ ማቅረቡ ቅኝ ገዥዎቹን በጣም አስበረገጋቸው። “ይህ ወጣት ዝም ተብሎ ከተተወ ከዚህ አካባቢ ሊያስነቅለን ነው” እንዲሉም አደረጋቸው። አልፎ ተርፎም ልጅ እያሱ በዘመኑ ከነዚህ ቅኝ ገዥዎች ጋር በአንደኛው የዓለም ጦርነት የሚዋጉትን ጀርመንና ቱርክን የመደገፍ አዝማሚያ ማሳየቱ ሶስቱ ሀያላን እርሱን ከስልጣን ለመንቀል በሚደረገው ትግል በቀጥታ እንዲሳተፉ አነቃነቃቸው።

በመሆኑም ሀያላኑ ጳጉሜ 1908 የእያሱን የጠላትነት እርምጃ በማስመልከት በጻፉት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ አድማውን መቀላቀላቸው ይፋ ሆነ። ከመጋረጃ ጀርባ ኩዴታ ጠንስሰው ወደ ተግባር መለወጥ ላቃታቸው የሸዋ መኳንንት ኩዴታው ወደ ተግባር የሚለወጥበትንም ስልት አስጨበጧቸው። በተለይ በእያሱ ላይ የቀረበው የመናፍቅነት ክስ ትክክል መሆኑን ለማስረገጥ የእያሱን መስለም የሚያሳዩ ፎቶግራፎችን እያባዙ በአዲስ አበባና በሌሎችም ከተሞች አሰራጩ። 
***** ***** *****
ይህ ውጥረት በተፈጠረበት ወቅት ልጅ እያሱ ኦጋዴን ነበር። ከበረሃ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ በቤቱ ላይ የተለኮሰውን እሳት እንዲያጠፋ ወዳጆቹ መልዕክት ቢሰዱለት “የሸዋን መኳንንት በአፉ ላይ ብሸናበት የሚናገረኝ የለም” የሚል የንቀት መልስ መለሰላቸው። በዚህም የስልጣን ፍጻሜውን አቃረበው። ታዲያ እያሱ የጠላቶቹን አሰላለፍ በደንብ የተገነዘበው አይመስልም። በርሱ ሐሳብ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ለማመጣጠን የሚወስዳቸውን እርምጃዎች የሚቃወሙት የሸዋ መኳንንት ብቻ ነበሩ።

ነገሩ ግን እንዲያ አልነበረም። ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ እንደሚሉት ልጅ እያሱ ፖሊሲውን በግልጽ ባለማብራራቱ ተራው ህዝብ እንኳ ሀገሩን ለማስለም ሌት ተቀን የሚደክም አድርጎ ነው የወሰደው። በዚህ ላይ እነ ደጃች ተፈሪ በቆንስሎቹ ድጋፍ እያሱ የሚገለበጥበትን የሀሰት ክስ ቀምመው ሲያቀርቡለት ህዝቡም እንደ መኳንንቱ “ድሮስ ከሙሐመድ ዓሊ ልጅ” አለና አረፈው። በመሆኑም ሰፊው ህዝበ ክርስቲያን ለዱለታው ድጋፉን ሰጥቷል። የእያሱ እጣ አሳዛኝ የሚሆነው ድሮ የሚገብሩለት ሁሉ በዚህ ቀውጢ ጊዜ ሲከዱት ነው። በተለይ በስልጣን ዘመኑ መጀመሪያ ላይ በወሰዳቸው ተራማጅ እርምጃዎች ተደስተው በርሱ ዙሪያ የተሰለፉት ለውጥ ናፋቂ ምሁራን በዚህ የፈተና ወቅት የገቡበት ሳይታወቅ ከጎኑ ጠፍተዋል። አንዳንዶቹ ጭራሽ ከርሱ ጎራ ተነጥለው እርሱን ወደ መንቀፍ ገብተዋል። ለዚህም ምሳሌ የሚሆነው የነጋድራስ አፈወርቅ ገብረኢየሱስ ነገር ነው። ነጋድራስ አፈወርቅ ልጅ እያሱን በስልጣን ዘመኑ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያ ተስፋና የለውጥ ሀዋሪያ አድርገው እንዳላንቆለጳጰሱት ሁሉ በዚህ የመከራ ወቅት እንዲህ የሚል ስንኝ መቋጠራቸውን ታሪክ አዋቂዎች በትውስታቸው መዝግበዋል።

ሙሐመድ እያሱ
ለገመ በራሱ
እያሱ ሙሐመድ
አልጋ ሲሉት አመድ።
(ብርሃኑ ድንቄ፣ ቄሳርና አብዮት፣ 1986፣ ገጽ 30)

እንግዲህ የልጅ እያሱ ውድቀት እውን ሆነ። ለሶስት ዓመታት የነገሠበትን አልጋ ከውጪና ከውስጥ በተሸረበበት ሴራ አጣ። መስከረም 17/1909 ዓ.ል. ዘውዲቱ ምኒልክ ንግሥተ ነገሥታት ተብላ ዙፋኑ ላይ ስትቀመጥ ደጃች ተፈሪ መኮንን “ራስ” ተብሎ የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ ሆነ። ይህ ሁሉ ሲከናወን ኢላማ የሌለው ተኩስ አልፎ አልፎ ከመሰማቱ በስተቀር አዲስ አበባ ሰላም ነበረች (አንዳንዶች 17 ሰዎች ሞተዋል በማለት ጽፈዋል)። 
***** ***** *****
የልጅ እያሱ ከስልጣን መውረድ ዜና የተሰማው እያሱ ጅጅጋ እያለ ነው። የዜናውን መሰማት ተከትሎ የእያሱ ደጋፊዎች በሚበዙባቸው ሀረርና ድሬ ዳዋ ታላቅ ረብሻ ተነሳ። የደጃች ተፈሪ መኮንን ደጋፊዎች የተባሉት እየተሳደዱ ተፈጁ። እያሱ በከተሞቹ ደርሶ ሁኔታውን ካረጋጋ በኋላ በአሻጥር የተወሰደበትን ዙፋን ለማስመለስ ከከተሞቹ ነዋሪዎች ጋር ተማከረ። በዚህም የህዝቡን ድጋፍ ካገኝ በኋላ በሸዋ ላይ ለመዝመት መዘጋጀት ጀመረ። ይሁንና ዝግጅቱን ሳያጠናቅቅ እነ ራስ ተፈሪ የላኩት 15,000 ጦር ወደ ሀረርጌ እየመጣ መሆኑ ታወቀ። ልጅ እያሱም የሸዋውን ጦር ለመግጠም ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ገሠገሠ። ሁለቱ ሀይሎች ሚኤሶ አጠገብ ተገናኙ። ትልቅ ውጊያም አደረጉ። በጦርነቱ የሸዋው ሀይል ድል ስለቀናው ልጅ እያሱ ወደ አፋር በረሃ ሸሸ። የልጅ እያሱ አባት (ራስ ሚካኤል) የልጁን ስልጣን ለማስመለስ 100,00 ጦር አስከትቶ ወደ ሸዋ ዘመተ። ነገር ግን እርሱም እንደ ልጁ ሰገሌ ላይ ተሸነፈ።
***** ***** *****
ልጅ እያሱ የሰገሌውን መርዶ ከሰማ በኋላ በሽሽት ነው የኖረው ለማለት ይቻላል። በመቅደላና በደሴ አነስተኛ ውጊያዎችን ቢያደርግም በለስ ሊቀናው አልቻለም። ከዚያም ወደ አውሳ በረሃ ሄዶ ከወዳጁ ከሱልጣን አቡበከር ጋር ለጥቂት ዓመታት ኖረ። ነገር ግን ጠላቶቹ እዚያም እንዲቆይ አልፈቀዱለትም። ከሀረርጌና ከወሎ ትልቅ ጦር ቢያዘምቱበት ወደ ትግራይ ሸሸ። በትግራይ ውስጥ ለጥቂት ወራት ከቆየ በኋላ በ1915 ተያዘና ፍቼ ታሰረ። እዚያ እያለ የጎጃሙ ራስ ሀይሉ ተክለሀይማኖት እስር ቤቱን ሰብሮ ሊያስወስደው መሆኑ ስለተወራ ሌላ ቦታ እንዲዛወር ተወሰነ። በመሆኑም ወደ ሀረርጌ ተወስዶ ጋራ ሙለታ አምባ ላይ በተሰራለት እስር ቤት እንዲታሰር ተደረገ። በዚህ አምባ ላይም ለአስር ዓመታት ያህል በእስር ከቆየ በኋላ ጥቅምት 1928 መሞቱ ይፋ ሆነ። 
***** ***** *****
ልጅ እያሱ ሚካኤል የስልጣን ዘመኑ በእንቆቅልሽ የተመላ ነው። መንግሥቱን ያስተዳደረበት ዘይቤ፣ ከስልጣን የወረደበት ሁኔታ፣ በእስር ላይ ያሳለፈው ህይወትና የሞተበትም ሁኔታ እንቆቅልሽ ነው። ሌላው ይቅርና የተቀበረት ቦታ እንኳ እስከ አሁን ድረስ በትክክል አይታወቅም። እንቆቅልሽ በእንቆቅልሽ! 

ተሸዋረጋ የሚወለድ ልጅ
እምብዛም አይከፋ እምብዛም አይበጅ
ትንሽ ወደኋላ ይቀረዋል እንጅ።
ባሽከሮቹ ክፋት ደግሞም ባጋፋሪ
ዘውዱ ሲዞር አየን ወደ ልጅ ተፈሪ።
እያሱ የሚባል አንድ ልጅ ተወልዶ
የአባቶቹን መሬት አደረገው ባዶ።
መች ባንተ ይሆናል ምኒልክ ንጉሡ
አንተ አስበህ ነበር ልትሰጠው ለእያሱ
እንኳን ሊነግሥና ይያዛል ለነፍሱ
በራስ መኮንን ልጅ ትጠፋለች ነፍሱ
ተጌታ ተፈርዷል ዘውዲቱ ሊነግሱ።
የልጅ እያሱ ሰው የአባሻንቆ ሎሌ
ተለቀለቀለት መወቂያው ሰገሌ።
ሰገሌ ሜዳ ላይ የመጣብን መርዶ
በቀኝ እጁ ካራ በግራው ብርንዶ።
(የወሎው ሼኽ ሑሴን ጂብሪል ስለልጅ እያሱ ተናግረውታል ከተባለው ትንቢት: ምንጭ፣ ቦጋለ ተፈሪ በዙ፡ “ትንቢተ ሼኽ ሑሴን ጅብሪል”፣ አዲስ አበባ፣ 1985)
***** ***** *****
አፈንዲ ሙተቂ
ሰኔ 15/2005 
በሀረር ከተማ ተጻፈ።

Tuesday, January 3, 2023

#Adama vs #Nathret

አፄ ኃይለስላሴ አዳማ ከተማ በ1937 ዓ/ም ናዝሬት ተብላ እንድትጠራ ያደረጉበትና በግድግዳ ላይ ስለ ናዝሬት ከተማ መስፋፋትና እድገት ያደረጉት አስተዋጽኦ በሚል በሃውልት ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ቀዳሚ መረጃ ነው። ይህንን ጽሁፍ በጥሩ ጥራት ባለው ካሜራ መነሳትና እንደ ቅርስም በደንብ መጠበቅ ይኖርበታል የአፄው ቡችሎች እንዳያፈራርሱት። አንድ ቀን ደግሞ ፊንፊኔን አዲስ አበባ ብለው የሰየሙበት መረጃ በራሳቸው እጅ እንዲህ የተፃፈ ይገኛል ታሪክ ተቀብሮ አይቀርም ባሻዩ ። 

#Abbaa _#jiffaar

𝐀𝐛𝐛𝐚𝐚 𝐉𝐢𝐟𝐚𝐚𝐫 𝐈𝐈

➊. Maqaan Isaanii Muhammad bin Daawud Jedhama.

➋. Nama Gaafa Ummanni Oromoo Dukkana Keessa Ture Mootummoota Addunyaatiin Wal Barsiise.

➌. Dhiira Dachii Biyya Isaa Bira Dabree Dachii Arabootaa Irratti Mana Rabbii Ijaarsise.

➍. Goota Itoophiyaa Keessatti Oromoon Mootummaa Ta’uu Akka Danda’u Barsiise.

➎. Nama Seenaa Oromoo Fi Islaamaa Keessatti Faana Dhiifatee Deeme.

➏. Mootii Qaroominaan Beekkamu. Gaafa Mootonni Habashaa Miila Qullaa Yaatu, Nama Silipperii Hojjachiise.

➐. Mootii Gaafa Ummanni Oromoo Lafarraa Duguugama Turetti, Haadha Manaa Hedduu Fuudhuun Karaa Ittiin Revive Godhan Barsiise.

➑. Mootii Jireenya Ummata Isaatii Fi Biyya Isaa Jijjiire.

#Dirre_#dhawaa

Dirree dhawaa. 
             ----------
Jecha Daha ykn dhawa ( dhawaa ) jedhu kana galmeen jechootaa  ( English- borana world list ) ykn vencent G. Stegmen kitaaba isaa keessatti jecha dubbachuu ykn waa himuu jedhuun hiikee jira. Bifa wal fakkaatuun fakkeenyaaf:- oromoon booranaa Haasawa isaanii  keessatti " Abaluu maal dhahata ? Jedhu,  oromoo booranaa qofaa mitti , naannoo harargetti yeroo hedduu  " gurbaan maal dhawachaa deema ? ykn qaallichi maal dhawata ?
Jedhu, kana jechuun maal dubbachaa deema 
Ykn maal jedha jechuu barbaadaniitii.
               Magaalaa dirree dhawaa keessatti,
Dirreen dhaha' ykn dhawaa  iddoo Amma dachaatuu irraa kaassee hamma ganda gaaraa jiru kana gubbaa  hoggaa tahu  oromoonni afran Qalloo iddoo kana maaliif lafa dhawaatiif filatan kan jedhuuf yaada bal'aa kaasuun ni dandahama. Haa tahu malee  qulqullina samiitiifi  Ripha lafaa ( Altitude) qofa laaluun iddoon kun hojii dhahatiif mijaa'a akka tahe salphatti hubbachuun ni dandahama. Kana qofaa mitii,
Dirreen tan gubbaa dhaabbachuun  wal qaxxaamura urjilee daawwachuun  hedduu mijaa'aadha.
              Irra caalaa dirree tana lafa dhawaatiif mijooytuu kan godhe dhaloota ji'aa handaara fugug keessatti ( moon under Horizon) arguudhaaf salphaadha.
        Magaalaa dirree dhawaa keessatti,waqtii afran jechuun birraa; bonna, ganna fi badheessa  keessa  Aduun sadarkaa ykn digrii adda addaatiin baati. Kanaan wal qabatee 
tulluu fi gaarreen adda addaa moggaasa 
Gara garaa qaban.
    Fakkeenyaaf guyyaa Arr'aa, galgala  kana, magaalaa dirree dhawaa bakka magaalaa ykn dachaatuu jedhamtu keessa dhaabbachuun  kallattii bahaa  digrii  67°  irratti         
Ji'a  Adeessaa  dhibba irraa harka 87.7 %  arguu ni dandeessa.  Noonnoo kanatti  Amajjii 7 irraa kaassee hamma 14tii guutuu guutuutti 
Ji'ini kan Goobanu taha. bara 2023, Ji'a Bittoteessaa ,
Guyyaa 21 irraa kaassee naannoo kanatti  badheessi kan eegalu hoggaa tahu harargee keessatti  iddoon hedduuun dur irraa kaassee Rooba badheessaa yeroo kana argachuun beekaman.... galgala kana keessa,  akka lakkooysa itiyoophiyaatti sa'aa 12: 20 irratti 
Plaaneeiii venus ,Saturn galgala sa'aa 2: 53 irratti samii magaalaa dirree dhawaa irratti arguu ni dandeenya .

Saturday, December 31, 2022

#Hiikaa_Maqaa#Gosoota ilmaan #Baareentummaa.

#Hiika Maqaa #Gosaa
★******************-****************★
#Baareentuu=Jiraattoota  warra bahaa kara aduun bariituun jiraatan jechuudha.

#Walloo=Waloo jechuudha, Walee, Tokkummaa jechuudha.

#Raayyaa = Raayyaan gurmooftuu, Loltuu, humna jechuudha.

#Kaarrayyuu= Kaarra Hayyuu Beektoota hayyoota Aadaaf duudha isaanii jabeessanii jajjabduu jechuudha.

#Waayyyuu: Waayyuun Kabaja jechuudhaa.

#Murawwaa = kan namatti tolu, Kan haasooyni isaa mi'aawu jechuudha. 

#Ituu = itiitaa, tasgabaawaa, beekaa namaa jechuudha.

#Baabboo = Kan Abbaa Fakkaatu, ykn kan hiiriira duraarra jiru jechuudha.

#Gaadullaa = Kan loon horsiifattu, Carraaqataa, ykn ka gadaaf duule jechuudha. 

#Galaan = Galaana, ykn ka Heeraan deemu, Kan waa adda galchu jechuudha.

#Algaayyo = Kan alaaf gahan, kan diinaaf gahan, ka ofiif gahu jechuudha.

#Qaalluu = Qajeelchaa, Gargaaraa, Masoo ofii jechuudha. 

#Waayyee = Injifataa, kan boochissu, kan kuffissu, kan waa tiiysu jechuudha. 

#Arroojii = Arjaa, ykn kan dafee dhaqqabu ykn nama dafee aaru jechuudha. 

#Addaayyoo = Saafii, Adii , Qulqulluu namaa jechuudha. 

#Gaamoo = Gammachuu kan qabu,bashaasha namaa, ykn warra gamtaa qabu jechuudha. 

#Baaye = turee dhufaa ykn Ba'eessa namaa jechuudha"
Link:- website
Mikysultan.blogspot.com

#Goota #Imam Yesuf_ #AbbaaMarchaa

Goota Imam Yasuf,( Abba Marchaa)
 #Aba Marcha Baxi#
***************★★★****************
/bymakinsulatn Wallo/.....
Gootni imam yesuf abba marchaa kan dhalate walloo baatee naannoo garfaatti yeroo ta'u, Ammas nama jabaa samaa gaadullaan qabdu keessaa tokko.
 Yeroo mootumma hayilasillase sani hanga mootummaa dargiitti goota beekamaaf sodaatamaa ture.

Abbaan "marchaa" maqaa farda  isaati yoo ta'u, dur goonni maqaa farda isaanitin waamamu turani.
Goonni imam yesuf abba marchaa goota yeroo hayilasillaasee mootii bulchaa  walloo qaalluu hanga warra himanootti bulchaa tureedha.
Ammas naannoon Affaarii magaalaa baatee jala bulaa turte magaalaa guddoo Awsaa taatee bulchaa turte. Affaaronni oromoota walloo jala bulaa turani. 

Ammas yeroo hayila sillaase san waraanni warra somaalota gosoota iisaa fii  affaari daran hamaa waan tureef affaaronni baqatanii naannoo baatee qubatanii jiraachaa  turani.
waraanni Somaale gosoota 'isaa' baayyee cimaa waan tureef affaar gara oromoota wallootti dheessaanii jiraachaa turani. 

Goonni Imam Yesuf Abbaa marchaa waraana isaa garfaaf waayyuu, qaalluu  ammas affaaroota of jalatti hirirsuudhaan  waraana somaalota gosoota isaa waliin godhee hanga lafa jabuutii magaalaa  "dikel" jedhamtutti waraana godheen  injifatee galee jira.

Ummanni affaari Maqaa isaatin dhaadataa  turani, Nuti ilmaan abbaa marchaati/ Abba marcha Baxi/ jechaa dhaadatu ture. 
Gootummaa isaatin  itti geeraru ture.
Hiriyyaan ISaa yeroo Sanii Umaree Muhee ture. Umaree Muhee Enyu?

Goota Umaree Muhee
************************************
Gootni Umaree muhee kan dhalte walloo baataa garfatti yoo ta'u ummata biratti goota kabajamaaf jaalatamaa ture.
ummanni naannoo baatee garfaa waayyuu maqaa umaree muheetin dhaadatu "Dhufte Ijoolleen Baatee Gudfisaan Umaree" jechaa dargoof dubareen maqaa isaatin dhaadachaa taphatu.
Umaree muhee goota ija barbadaa diinaaf gadin jenne ture. 

Suuraa isaa argachuu hin dandeenye yoo argame ka umaree muhee akkuma arganneen maxxansina seenaa guutuu isaa wajjiin.

Thursday, December 29, 2022

#imam yesuf/Abba Marcha/#ኢማም የሱፍ_አባ መርቻ።

#ጀግና ኢምም የሱፍ(አባ መርቻ)
#imam Yesuf (Abba Marcha)
#አፋሮች የምሟገሱበት፣አባ መርቻ ( ኢማም የሱፍ)
---------------------------***---------------------------
     √*Abba _Marcha Baxi -- *

/By Makin Sultan Wallo/
ኢማም የሱፍ አባ መርቻ፣ በ ወሎ ክፍለ ሀገር፣ በባቲ ወረዳ ገርፋ ተወላጅ ስሆን። በ ገርፋና ዋዩ እስከ ወረ ሕመኖ ሀገር ገዢ ነበረ፣ በ ንጉስ ሀይለስላሴ ግዜ፣ኢማም የሱፍ በፈረሰቸው ስም አባ መርቻ ተብሎ ይጠሩ ነበረ። አባ መርቻ በጣም ጀግና ሀይለኛ ለማንም የማይበገሩ ጀግና የወሎ ሰው ነበሩ።አፋሮች የ አባ መርቻ ልጆች ነን እየሉ በ ስሙ  ይጠረሩበት ፣ይሟጋገሱበትነበረ። አባ መርቻ ፣በ ንጉሰ ሀይለስላሴ ግዜ የ ሶማሊ ጎሳ የሆኑት ኢሳዎች አፋሮችን ያስቸገሩ ስለነበረ። አፋሮች ወደ ባቲ መጥቶ ይኖሩ ነበረ።
አባ መርቻ የወሎ ባቲ ኦሮሞ ገራፋ ዋዩን፣አፋሮችንም  ጦር አሰልፎ  እስከ ዲኬል የምትባል ከተማ  ጅቡቲ ኢሳ ጎሳዎች ጋ ተዋግቶ ድል አድርጎ የተመለሰ ጀግና ነበረ። አፋሮች ለዚያ ነው፣ ኢማም የሱፍ እንደ አባት አድርጎ  ኣፋሮች የ አባ መርቻ ልጆች ነን እየሉ በ ገጠር ጫውታ ሙገሳ ላይ በሱ የምሟገሱበትና የምጫወቱት ፣የ አባ መርቻን ጀግንነት ስለምያውቁና ስለዩ ነው።
የ ኢሳ ጎሳ ሶማሊ ጦር አባ መርቻ ጦር በዚህ ገብቷል ከተባለ በጣም ይፈሩ ነበረ። ኢማም አባ መርቻ ቀጭን ሀይለኛ ለማንም የማይበገሩ፣ የወሎ ባለባት ሀገር ገዢ ነበሩ። በነ ኢማም የሱፍ ግዜ በጣም ጀግና እሳት የላሱ ጎደኞችአብሮት ነበሩ፣ ለምሳሌ የባቲ ሰው በስሙ የምሟገስበት ጀግና ኡመሬ ሙሄ የምባል ጀግና የባቲ የገርፋ ሰው ነበረ።የባቲ ሰው ጫውታ ላይ የአመሬን ጀግንነትን ስገልፅ /dhufte ijoolleen baatee guddusaan umaree/ እያሉ በስሙ ይሟገሱበታል። ትርጉሙ መጣ የባቲ ልጅ ጀግና የ ኡመሬ ትውልድ፣ልጅ ማለት ነው። አፋሮች ጭምር በባቲ ኦሮሞ ጀግኖች እኛ አባ መርቻ ልጆች እያሉ ራሰቸውን በጀግና ስምበ አባ መርቻ ኢማም የሱፍ ይጠሩ ነበረ።
ባቲ የዚያን ግዜ፣ ወሎ ክፍለ ሀገር አውሳ አውራጃ ነበረች፣የ ወሎ ጥንት ከተማና የአፋር ዋና ከተማ ነበረች። አፋሮች በባቲ ስር ይተዳደሩ ነበረ። ዋና መስርያ ቤተቸው አሳይታ ነበረ።

»|*|«  ኢማም የሱፍ  አባ መርቻ»|*|«   (( ገ ር ፋ  ))

= ኢጆሌ ገርፋ  ፣ የጦር መድሃኒት =

= እንኳን  ቀንና  ፣ ይዋጋል ሌሊት  =

:

= ጀግናው ሲጋልብ ፣   በላይ ፈረሱ  =

= አስደሳች   ነበር   ፣ ግርማ ሞገሱ =

:

= ግርማው አስፈሪ ፣ የዳልግ አንበሳ =

= ኢማም የሱፍ ነው ፣  የ ማ ይ ረ ሳ =

by #miky sultan_wallo

by #miky sultan_
Website:-https://mikysultan.blogspot.com/?m=1
Youtube gallee subscribe haa goonu.
https://youtube.com/channel/UC28cmklQecQdOikbnwfG8XQ
https://t.me/+5lATA7899SU3OGM0
Nu dubbisuu yoo barbaadan:- @Mikysultan1
https://www.facebook.com/wallo.lion.9?mibextid=Z

mootittii saba'a Queen of sheba

"Mootittii Saba'a""Queen sheba" ----------------------------------------------------------------- ★Miky Sultan Bar...