Translate

Saturday, February 26, 2022

#ራያ ገረብ ኦዳ/# Raya Oda

ገረብ(ሓንስ) ኦዳ የአባቶች ጥላ 🌳🌳🌳🌳🌳🌳🌳 #በራያ አላማጣና አካባቢዋ #ገረብ የሚባል የሽምግልና ስነ-ስርዓት እንዳለ እውቅ ሆኖ እነዚህ አባቶቻችን ለነፍሳቸው ሲሉ ወንድም ከወንድሙ ሲጋጭ አንተ ተው አንተ ተው እያሉ እያስታረቁ እና እያስማሙ ራዮችን አንድ እያደረጉ እያፋቀሩ ለዘመናት ኖረዋል፣ አሉ ይኖራሉም። እነዚህ አባቶች ፈጣሪ በሰጣቸው ለምለም ጥላ ሁነው ሽምግልናቸውን ሲያካሂዱ ቆይተዋል ነገር ግን በዚህ ሰዓት የሚጠለሉበት ቦታ ወድሞና ሌላኛው ደግሞ ወድቆ እየተቸገሩ እንዳሉ እያየን ነው። ለምሳሌ ይሀክል በራያ አላማጣና አካባቢዋ የዕርቅ ስነ-ስርዓት የሚጠቀሙበት ዋናዎቹ #ዓውዪ_ኦዳ እና #ሓንስ_ኦዳ እየተባሉ የሚጠሩ ሁለት አንጋፋ ጥላዎች ሲሆኑ፤ ዓውዪ ኦዳ እየተባለ የሚጠራው ስመ ገናናው የአባቶች ጥላ በቅርብ ዓመታት ወድቆ ከጥቅም ውጪ ሁኗል። ሌላኛው ደግሞ ሓንስ ኦዳ እየተባለ የሚጠራው ለህብረተሰቡ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት እየሰጠ የነበረ ሲሆን ከነዚህም ሁሌ አዲስ ዓመት ላይ ማህበረሰባችን ከከተማውና ከገጠሩ አሰባስቦ በፍቅር የሚውልበትና እሸት ጥንቅሹ እየተበላ ባህላዊ የራያ ዘፈኖች እየተዘፈኑ ትግል እየተታገሉ እየተጫወቱ የምያሳልፉበት ቦታ ነው። ሌላኛው ዋነኛው ጥቅሙ ደግሞ ብዙዎች ሲጣሉና ሲጋጩ አባቶች የዕርቅ ስነ-ስርዓት የሚያካሂዱበት ትልቅ የተከበረ ጥላ ነው። ስለዚህ ወገኖች እኔ ይህ ፕሮጀክት ከጀመርኩት የቆየሁ ብሆንም ነገር ግን አሁን ተቀናጅተንና ተጋግዘን ለሰላማችንና አንድነታችን ለቆሙልን የአባቶች ጥላ ብናስከብርላቸው አይበዛባቸውምና ካሁን ብኋላ ላለው ብንተጋገዝ ምን ይመስላችኋል

#ኦዳ ገራዶ( ዋርካ) #Odaa Gerado

<< የ ኦዳ ገራዶን ታሪክ >> "ኦዳ ገራዶ" አባቶችን ስንጠይቅ የሰጡን ምላሽ >> በዛ የብሄር እና የሃይማኖት እኩልነት ባልነበረበት በአስከፊው የፊውዳል ስርአት ዘመን የወሎ ኦሮሞዎች ላይ ይደርስ የነበረው ስቃይና በደል እጅግ ከፍተኛ ነበር እናም ከዚህ አስከፊ ሁኔታ ራሳቸውን ፣ታሪካቸውን (ማንነታቸውን) ለመጠበቅ ራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩበት የ"ገዳ" አይነት ስርአት ነበራቸው ። እናም በዚህ በምታዩት ዋርካ ስር በመሰባሰብ በማህበራዊ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ይወያያሉ ፣ ህግ አርቅቀውና አፅድቀው ለማህበረሰቡ አዋጅ ይናገሩበታል፣ ራሳቸውንም ከጠላት እንዴት መከላከል እንዳለባቸው ይመክሩበታል ፣ ያጠፍ ሰዎችን ዳኛ ሰይመው ይቀጡበታል ፣ የተጣሉትም ግለሰቦች በዛፍ ስር ተሰባስበው ያስታርቁበታል ። እንደው በጥቅሉ "ኦዳ ገራዶ" የወሎ ኦሮሞዎች የ "ፖርላማ" መእከል እንደነበር ታሪክ ይመሰክራል ። ኦዳ ገራዶ የሚገኘውም በወሎ በኦሮሞ ዞን ዋና መዲና በሆነችው ከሚሴ ከ "ሒጅራ" መንደር ከፍ ብሎ ከ "ቀሎ" ቀበሌ ዝቅ ብሎ ወደ አዲስ አበባ በሚወስደው በዋናው አስፖልት ዳር ነው ።

Friday, February 25, 2022

#Yejju/#የጁ

#የጁ የየጁ ኦሮሞ ህዝብ የባሬንቶ ቅርንጫፍ ንኡስ ጎሳ ነው ። እነሱ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚኖሩት በሰሜን ካሉት የኦሮሞ ህዝብ ማህበረሰቦች አንዱ ናቸው።የጁ በ ሰሜን ወሎ መረሳ፣ጉባ ላፍቶ፣ሐብሩና እስከ ሰዶማ ሀረና ሀሮ፣ ድሬ ሮቃ እስከ ጃራ በ ሰፊው የምኖሩ ሕዝቦች ናቸው። በ17ኛው ክፍለ ዘመን የየጁ ስርወ መንግስት በተለይም የዋራ ሼክ ወይም የሼኩ ልጆች በዘመነ መሳፍንት ወይም "ዘመነ መሳፍንት" ጊዜ አብዛኛውን የኢትዮጵያ ኢምፓየር ያስተዳድሩ ነበር፣ በጎንደር አደባባይ የነበረውን ቋንቋ ወደ ኦሮምኛ [2] በዘመኑ የተለያዩ ብሄረሰቦች፣ ጎሳዎች እና ማህበረሰቦች ኢኮኖሚያዊ ጥቅምን እና የፖለቲካ ስልጣንን ለማግኘት የአጭር ጊዜ ጥምረት ፈጥረዋል።የየጁ ስርወ መንግስት ገዥዎች ወደ ክርስትና የተለወጡ ቢሆንም የስልጣን መሰረታቸው እንደ የጁ፣ ወራ ያሉ ኃያላን የወሎ ሙስሊም ርዕሰ መስተዳድሮች ነበሩ። ሂማኖ እና ራያ። እ.ኤ.አ. በ1890 ዓ.ም በዳግማዊ ምኒልክ ዘመነ መንግስት የየጁ የትውልድ ሀገር ለነሱ ተብሎ በኢትዮጵያ ግዛት (አውራጃ) ተደራጅቷል። በሰሜን በኩል ከአለውሃ ወንዝ ጋር ትዋሰናለች፣ ከራያ ቆቦ አውራጃ፣ ወደ ደቡብ ከሚሌ ወንዝ በመለየት፣ ወራ ባቦ ወረዳን፣ የአፋር ጭንቀትን በምስራቅ፣ እና ደጋውን የአምባሰልን ወደ ምዕራብ ። ወልድያ የየጁ ዋና ከተማ ሆና አገልግላለች። በ1994 የብሄረሰብ ፌደራሊዝም ጸድቆ የአውራጃ አስተዳደር መዋቅር ሲወገድ የጁ በሐብሩ፣ ወልድያ ከተማ እና በጉባ ላፍቶ መካከለኛ ከፍታ ባለው ክፍል መካከል ተከፋፈለ። ከ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ጀምሮ የየጁ ኦሮሞዎች ወደ ዋናው የሴም ሕዝብ ባህል በመዋሃዳቸው ምክንያት በአሁኑ ጊዜ በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኙት የጁ አማራዎች ናቸው ብለው ይጠሩታል ግን ኦ ርጅናሊ ሕዝቡ ኦሮሞ ነው።

#Shanan #Jiilleef#Saddeen #Makkannaa Walloo

Shanan jiilleef Sadeen Makkannaa ************************************* Annan jillee dhummuugaa Bara 1994 Akka LI Aanaa taatee hundooftee” Kaaban Aanaa harxummaa fursee.bahaan naannoo Affaar Kibbaan Aanaa Qaawwai dhihaan ifraataa gidimiin daangeffamtti, Yeroo ammaa gandoota 24 ol qabdii jedhama akkasuma Bulchiinsa magaalaa 1 qabdi. Magaalaan guddoon isaanii magaalaa Sanbateeti.Ummanni baay’inaan Magaalaa kana keessa jiraatu Shanan jiilleeti fi Sadeen Makkannaati jarri lamaan obboleeyyanii, Ilman shanan Jiillee 5nii, Jiillee ilma karrayyuu Bareentooti 1,ABBO 2,KARRAYYUU 3,BALA’A 4,LIIBAN. 5,WARRA QAALLUUTI Sadeen makkannaa jechuun makkani kan dullachaa Bareentoti Ilmaan sadeen Makkannaa (3″sadii) 1,ABBAADHO 2,NOOLE 3,GUTAA. gabayaan sanbatee kuni magaalaa guddoo Aanaa Kana keessatti argamti gabayaan guddaan kuni torban keessaa guyyaa Sanbataa guddaa dhaabbata. namoonni biyya fagoo jiran jala bultii waan dhufaniif baay’ina namaatiin guutamtee oolti. bal’inni lafa gabayaa Sanbatee heektaara 1.7825 yookiin karee meetira 17825 ta’a jedhamee Dubbatamas. Baay’inni ummata magaalaa Sanbatee 14475 ta’a Jedhama, Gabayaan Sanbatee gabayaa baay’ee bal’aa fi iddoowwan gabayaa gurguddoo biyya keessa jiran irraa kan adda taasisu sabaa fi sablammoonni adda addaa afurii ol gabayaa kana waan haajoman Bitachuuf ni dhufu. Sabaa fi sablammootni afran kunniin saba Oromoo, Amaraa, Argobbaa fi Affaari. Saboonni kunniin hundi isaanii uffata aadaa isaanii calaqqisiisu uffachuu fi meeshaalee miidhaginaaatin faayamanii Bareedanii Aadaa isaanii qabatanii argamu. Gabayaa kanarratti faaya miidhaginaa fi firiiwwan ogummaa harkaa baay’inaan waan dhufaniif gabayaa kanaa bareedina addaa kanna bitachuuf bakkeewwan gargaara irraa sablammoonni hedduun ni dhufu magaalaa finfinnee irraallee kan dhufan ni jiran. Karaa biraatiin. Magaalli kuni kan Sabaa fi sablammoonni hedduun filannoo Godhatanii keessa jiraachaa jiraniidha tahuus lafni kuni kan Oromooti magaalli kun dachee Qotee Bultoota Oromoo irratti hundooftee. Gabayaa kana malees Aanaan kuni Akkuma godina fi biyya keenyattis seenaa baay’ee qabdii Aanaan kuni iddoowwan seenaa Qabeessa tahan (3″sadii) qabdii, “Isaanis kanneenii 1,fakkeenya yoo fudhanne baargamoowwan Lij Iyyaasuun Bara Bulchiinsa isaa Walloorraa yeroo gara finfinnee deemu harka isaatiin dhaabe gabayaa kana qarqara waan jiruuf namoonni biyya alaas ta’ee biyya keessaa baay’inaan gabayaa kana dhufanii daawwatu. Akkasuma ummata magaalaa fi Aanaa kana keessattu ummata shanan Jiillee jedhamuu biratti iddoo guddaa qabdi Baahargamoo lij Iyyaasuu kan bukkee isa dhadacha Aadatu jira bakka seerri ittin bulmaataa ummata kana itti tumamaa ture waggaa torba torban wal gahiin seera baasa turan. akkasuma bakka kana bishaan “Qabii Caffee” jedhamutuun jira Caffeen Oromoo biratti iddoo guddaa qabdi. Bakka kanatti Ammallee Ummanni shanan Jiillee yeroo rakkoon uumamee fii haala ittin jireenya isaa wal mari’achuu yeroo barbaade bakkuma kanatti Caffee irratti wal gahuun marii geggeessaa Akkasumatti Abbaa dhiiraatin hoogganamu seera Abbaa ormaa jedhu akkas jechuun seera Oromoo “seera abbaa gadaa” jechuudha haala kanaanis tokkummaa isaanii eeggachuun Aadaa ofii Amantii ofii tiksuun hardha gahaniiru, 2,Masgiida faqii Abbaas kan jedhamu Aanaa kana keessatti argama. 3,Bishaan hawweetu bishaan kuni maqaa baay’ee qaba namonni maqaa adda addattin yaamu namoonni tokko tokko hoo’ituu jedhu gariin gashaa jedhu akkasumas haweetu jedhu nuti amma “Hawwatuu” kan jedhu yaa fudhannu bishaan hawweetuu qabeenya Uumama baay’ee nama hawwatuudha . .

Wednesday, February 23, 2022

#Jaal #Buruuysoo _#Boruu

👉SEENAA JAAL BURUUYSOO BORUU ☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆ Seenaa dagannuus seenaan nama hin dagattu ! ~ Seenaa qabsaawootaa fi hogganoota bilisummaa Oromoo beekuun nurratti dirqama, keessattuu seenaa akka Jaal Buruuysoo kanafaa jechuudha. ~ Hanga maayyitti obsaan dubbisaa Share waliif godhaa ~ Jaal Buruusoo Boruu eenyu??? Jaal Buruuysoo Boruu ilma Oromoo qabsaawaa sabaa hogganaa ABO kan tureedha. ~ Jaal Buruuyso Boruu maqaa warri baaseef Abdulmaalik yoo ta’u Abbaa isaa Umar Abdushakuur fi Haadha isaa Raaziyee Haajii irraa Bara 1957tti baha Oromiyaa Harargee Bahaa koonyaa Gaara mullata magaalaa Baddannootti dhalate. eega yeroo inni dhalatu akkuma aadaa Oromootti, fira,maatii fi ollaan hundi haa guddatu, guddatees haa beeku,beekees lammiif kan ta’u haa godhu jedhanii eebbisan, eebbifamees hin hafne, eebbi isaanii milkaawuun innis akkuma guddatee lafaa ka’een lammii boonsuu jalqabe. ~ Jaal_Buruuysoo_Boruu dhalatee umriin isaa akka barnootaaf gaheen barnoota isaa mission naannoo sanitti argamutti kutaa 12 barate. ~Jaal Buruuysoo Boruu qabsoo diddaa gabrummaa Oromiyaa keessatti gaggeeffamaa ture irraa qooda fudhachuun nama guca qabsiise ta’uun hanga har’aatti yaadatamaa jira. ~ Lammiin Oromoo akka mataa ol qabatee eenyummaa isaatiin jiraatuuf namoota wareega qaalii kafaluun faajjii tahanii mataa ol qabachiisan keessan keessatti ramadama. ~ Gooti kun goota Oromoon hoggayyuu yaadattu goota sabaaf of wareegeedha. ~ Jaal Buruuysoo Boruu miseensa Adda Bilisummaa Oromoo(ABO) dirree qabsoo fi biyya jidduu nama hojjechaa tureedha. ~ Jaal Buruuysoo Boruu bara 1978tti dirree qabsoo seenee qabsoo hidhannootti makame, akkuma dirree qabsoo seenee leenjii fudhateen damee siyaasaa jalatti ramadamuun hojii barruu hojjechuu jalqabe. ~ Bara 1979tti yeroo Korri sabaa ABO taa’amutti koree qindeessituu keessatti ramadamuun barreessaa koree tahee filame, hanga wal gahiin hatattamaa koree jidduu bara 1984tti wal gahiin taa’amutti akka barreessaa fi WBOtti hojjechaa ture, wal gahii bara 1984tti taa’ame irratti Jaal Buruuysoo Boruu miseensa waajjira siyaasaa tahee damee dantaa Siyaasaa irratti hogganummaan filame. ~ Bara 1989 keessa yeroo korri Sabaa ABO irra deebi’amee taa’amutti Jaal Buruuysoo Boruu adda durummaan koree qindeessituu Kora Sanaa tahuun filame, ammallee irra deebi’uun barreessaa walii galaa kora sanaa tahuun filame. ~ Kora kana irrattis Jaal Buruuysoo Boruu damee siyaasaa irratti hogganummaan filamee dirqama isaa bahaa ture. ~ Bara 1990 keessa Jaal Buruuyso Boruu hojii diploomaasiitiif gara Soomaaliyaatti imale, hijii diploomaasii cinatti hojiin boonsaan jaalli kun hojjete keeysaa gurguddoon dhiheessi humna bahaa yeroo gabaabduu keessatti furuu isaatin kan yoomiyyuu yaadatamuudha. ~ Hanga biyya soomaaliyaa turetti humna ABO yeroo sanitti soomaaliyaa ture karaa taliiga bulchiinsaa,leenjisuu, hidhachiisuu fi bobbaasa qindeessuu irratti qoodni jaalli kuni gumaachaa ture guddaa dha. ~ Jaal Buruuysoo Boruu bara 1991 keessa yeroo mootummaan Ziyaad_Barree aangoo irra fonqolu waraana, miseensootaa fi deeggartoota ABO kan soomaaliyaa jiranii fi ilmaan Oromoo hunda akkasuma deeggartootaa fi miseensoota IFLO( Kan Jaarraa Abbaa Gadaa) jechuudha kan yeroo sanitti rakkoo ABO fi IFLO jidduu jirtuuf haala lolaa hamaa keessa waliin turan hunda wal dhabbii sanaaf osoo bakka hin kennin Oromummaa dursuudhaan IFLO dabalatee ilmaan Oromoo hundaaf akka karaan toolfamuu fi balaa achitti isaan mudate jalaa akka dandamatan godhuuf murtiin inni fudhate kan sadarkaa bilchina hogganummaa isaa agarsiisuu fi mirkaneessuudha. ~ Jaal Buruuysoo Boruu bara 1991 baatii caamsaa keessa yeroo Soomaaliyaa dhaqetti wal gahii kora jidduu ABO irraa qooda fudhachuun isaa ni yaadatama. ~ Wal gahii sanaan booda mootummaan #Dargii kufuuf biiyti waan jeeqamtee jirtuuf, haala jeeqamiinsaa san ilaaluun kufuu/Caphuun mootummaa dargii beekkame, eega yeroo kanatti kufaatii dargii kanaan ABO Oromoo akka biyya dhuunfattuuf hojii dhaaba ABO kan dirree bahaatti hojjatamtu hunda Jaal Buruuysoo Boruu ABO bakka bu’uun gaggeessaa haggana tureedha. ~ Bara 1991_1992 hanga ABOn mootummaa cehumsaa keessaa bahutti gaafatama waajjiroota ABO bahaa hunda fudhachuun, marii ABO fi TPLF jiddutti deemaa ture hunda ABO bakka bu’uudhaan nama gaggeessaa tureedha. ~ Yeroo sanitti karaa ajajoota TPLF shira walii galtee yeroo sanii diiguuf mata jabeenya fi moormii goggogduu warri TPLF oofan hunda gootummaan dura dhaabbatee falmaa hadhaawaa gaggeessaa waan tureef bara 1992 keessa humni TPLF Jaal Buruuysoo Boruu wajjiin haasoofnee rakkoo jirtu furra jechuun waajjira ABO magaalaa Harar(Adaree Biyyoo) tti maristee ajjeessuuf karoorfatte, haa tahu garuu iccitiin sun waan jalaa ba’eef ykn jalaa dhaga’ameef osoo itti hin milkaawin hafuun Jaal Buruuysoo Boruu humna waardiyaa isaa wajji gara magaalaa #Malkaa_Rafuu (Kombolcha) tti jalaa miliqee osoo hin turin gara dirree deebi’e. ~ Jaal Buruuysoo Boruu hagganummaa isaa cichoomminaan itti fufuun bara 1993 keessa yeroo hayyu dureen ABO yeroo sanii Jaal Galaasaa Dilboo gara biyya alaa yeroo bahu, bakka isaa bu’uudhaan akka hayyu dureetti gaafatamaa dhaabaa walii galaa fudhachuun hojjechaa ture jaal Buruuysoo Boruu. ~ Bara 1993_1995 jiddutti dura taa’aa walii galaa tahuudhaan taliiga bulchiinsaa gaafatama walii galaa tahuudhaan hogganaa osoo jiruu guyyaa 10/05/1995 tti lolli hamaan mooraa inni jirutti itti tahuun Jaal Buruuysoo Boruu murtii mataa isaa fudhachuun harka diinaa seenee qabamee wareegamuu irra jedhee murtii mataa isaatiin ofii isaatiif boombii lama ofitti dhoosee of wareeguun qabsaawootaa fi ilmaan Oromoo isa booda hafan hundatti kabajaa godhee wareegamee, qabsaawoota, deeggartoota, sabboontootaa fi ilmaan Oromoo hundatti sheenaa bara baraa tahee hafe. ~ Jaal Buruuysoo Boruu yeroo lubbuun jirutti miseensoota WBO,hogganoota fi deeggartoota dhaabaa akkasuma ummata Oromoo biratti nama kabajamaa fi Jaalatama ture. ~ Jaal Buruuysoo Boruu nama sirna,heeraa fi seera dhaabaa kabajee kabachiisuu irratti fakkii gaarii tahee hojjechuudhaan beekkama. Jaal Buruuysoon miseensoota WBO biratti akka hogganaa qofa osoo hin tahin akka Barsiisaa,Abbaa fi obboleeyyaniitti ilaalama ture, walumaa galatti yeroo hunda ganamaa fi galgala, yeroo deemu, yeroo taa’uu fi dhaabbatu hunda Furmaataa fi bilisummaa Dubbachaa, yaadaa, akkasuma nama hojjechaa ture tahuu isaa seenaan isaa ni dubbatti. ~ WAA’EE JAAL BURUUYSOO ILAALCHISEE JAALLAN LUBBUUN JIRAN KAN ISAA WAJJI TURAN KEESSAA HAMMA TOKKO YAADA ISAANII KANA DUBBISAA. Jaal_Urjii_Dhaabaa akkana jetti, Bara 1995 keessa Jaal Urjii Dhaabaa yeroo saniif miilaa dhawamtee madoo taatee mooraa Jaal Atoomsaa turte, xalayaan hatattamaa itti dhufuun gara Jaal Buruuysoo akka deemtu murtaawe yeroo kanatti jaallan isii wajji jiran Gaangee irra miila ishee diriirsuun kaayanii, yeroo Gaangee dadhabdetti qonyee irratti ba’atanii Jaal Buruuyso biraan gahan, akkuma achi dheeyxee toorbaan gaheen lolli hamaan mooraa Jaal Buruuyso keessa jiru kanatti itti tahee Jaal Buruuuysoo Boruu ishee biratti wareegame, haala inni itti wareegame yeroo ibsitu. ~ Seenaa qabsoo keessatti takka lolli hamaan akkasii isaan qunnamee hin beeku, akkasuma namni hanga Jaal Buruuysoo Boruu lolee lochiise wareegamee beeku akka hin jirretti ibsiti. ~ Jaal Buruuysoo Boruu Jaakkeeta ofirraa baasee T-Shirt Adii Alaabaa qabuun haa mul’attu jedhee lolaa ture, yeroo sanitti humni TPLF qabdu waan guddaa taheef Jaal Buruuysoo boruu akka jalaa miloqee hafuuf jaallan yeroo gaafatan wanni inni deebiseef kan daran gootummaa isaa agarsiisu ture, akkana jechuun deebiseef. 1, Jaallan na dura wareegaman lubbuu 2 wayii qabanii, anis lubbuma akka isaan qabaniitin qaba. 2, Humni Tigree kuni gootummaa nurra qaban moo humna nurra qaban? Jechuun cichoomminaan lolee lolchiisuu ture. Jaal Buruuysoo Boruu guyyaa lolli kuni itti ta’etti lafti inni ture gammajjii hamtuu waan taateef buseen nyaattee akka malee dhukkubsachaa osoo jiruu, yeroo lolli itti tahutti mirqaana qabuun hayyoota Tigree lola sana keessa jiran 3 . Abraha Siyyee..fi kkf gootummaa isaatiin harkaan qaqqabuun Qawwee(Girnoofa) isaanii harkaa fuudhee hunda isaanii walirra kaaye, Lola kana keessattis Jaal Buruuysoo eega harkaa dhawamellee gootummaan loluun maayyii irratti Tigreen humna dabalataa Helikoptariin akkasuma garaa Burqaatiinis tahee karaa fiilinis ol neeyxee humnaa ol itti tahuun Jaal Buruuysoo Boruu Asrii guyyaa 10/05/1995 tti harka kiyya diinatti hin kennu jechuun boombii ofitti dhoosee of wareeguu isaa qabatamaan waan bira jirtuuf ibsite, Dabalataanis Jaal Urjii Dhaabaa yeroo waa’ee jaal Buruuyso ibsitu Jaal Galaasaa Dilboo yeroo gara biyya alaa deemutti hayyu durummaa isarra kaaye deeme waan taheef akka hayyu duree ABOtti ilaalama jechuun dubbattee jirti. Gama biraatiin Jaal_Damissee_Kabbadaa yeroo waa’ee jaal Buruuysoo ibsu. Jaal Buruuysoon nama waahiloota isaa biratti kabajaa fi jaalala guddaa qabaachuu bira dabree barsiisaa tahuu isaa dubbata. Jaal Buruuyso biyya ollaatti diploomaasiif ramadamee deemuu yeroo murtaawe hojjechuu isaa erga dubbateen booda, hanga isarraa eeggamee ol Barsiisuu, karaa bahaa fi galaa qopheessuudhaan, hamma ammaatti Jaallawwan isaa kan isa yaadatu tahuus dubbata. Kanaafis Jaal Buruuyso goota kutataa, goota amanamaa tahuu isaatiin akka beekkamuus dubbatee jira jaal Damisseen. Jaal Damisseen itti dabaluunis Jaal Buruuyso Boruu dhuma bara 1991 fi jalqaba bara 1992 keessa lola hamaa guyyaa 15 deeme irratti adda durummaan nama gaggeessaa tuhuu isaa dubbatee jira. Wal gahii araaraa bara 1992 keessa ABO fi TPLF jiddutti taheen Jaal Buruuyso ABO bakka bu’uudhaan waaj dhufeef anilleen guyyaa san isa arguudhaaf carraa argadhe jechuun goolaban jaal Damisseen. Dabalataanis Jaal_Aslii_Oromootis akkana jechuun ibsiti waa’ee Jaal Buruuysoo Boruu, Jaal Buruuysoo Boruu haggana cimaa fi dandeeytii qabuudha, bara 1991 keessa Ana fi Jaal Buruuyso akkasuma Jaal Caalaa Leencoo yeroo gara soomaaliyaa deemnutti gaafatamni walii galaa ABO fi IFLO Jaal Buruuysootti kennamuu ibsiti Jaal Aslii_Oromoo. Eegaa waa’ee Jaal Buruuysoo_Boruu barreessanii fixuuf hedduu ulfaata kanaaf seenaa isaa hamma tokko keessaa bifa barruutiin isiniif qopheesse. Dabalataanis warri seenaa isaa bal’inaan beeytan seenaa goota keenyaa kana hanga irraa hafe itti nuuf guutaan dhaamsa kiyya. Share waliif gochuu akka hin daganne. Qabsaawaan ni kufa qabsoon itti fufa!!! Jaal Buruuyso_Boruu rabbi jannataan haa qananiissu.

Monday, February 14, 2022

#somali_ girl

የባህል ጌጣጌጥ እና የፀጉር አሠራር ያላት የሶማሌ ልጅ t.me/Oromo_geography

#አፍሪካዊት ሴት

አፍሪካዊት ሴት አርቲስቶች/ሰሪዎች፡- ፓስካል ሴባህ (ቱርክኛ፣ 1823 - 1886) Jean Pascal Sébah (ቱርክኛ፣ 1872 - 1947) ባህል፡ ቱሪክሽ ቦታ፡ ኑቢያ፣ ግብፅ (ቦታ ተፈጠረ) ቀን፡-ወደ 1878 ዓ.ም t.me/Oromo_geography

Sunday, February 13, 2022

#አባ ቦና ማነው?

<አባ ቦና> ማነው? <አባ ቦና> የሚለውን ቃል በሁለት የተለያዩ ታሪኮች ነው የማውቀው የመጀመሪያው በራያ የሚታወቁት የኩቢ አባቦና ስም ነው። . ዓጤ ዮሀንስ በአዋጅ ራያ ላይ ባካሄዱት ዘመቻ በእርሳቸው ግፊት ወደ ክርስትና የተቀየሩትን የአካባቢውን ገዥወች “ለጉዳይ ፈልጌህ ነው ሰውን ሰብስበህ ጠብቀኝ” እያሉ መልእክት በመላላክ እንጎየ ሜዳ ተሰብስቦ የጠበቃቸውን ወደ 3000 የሚጠጋ የራያ ሰው በአንድ ቀን እንደጨፈጨፉ ታሪክ ያወሳል። በወቅቱ አብረው የተገደሉት የሕዝቡ መሪ "ኩቢ አባቦና" በመባል ይታወቃሉ። አትመነው ትግሬን ቢምል ቢገዘት ክርስትና አንስቶ ኩቢን አረዱት የሚል ስንኝ ከኩቢ አባ ቦና ሞት በኋላ የራያ ሰወች ቋጥረዋል፤ ለትውልድ ተላልፎ ዛሬ ድረስ ይነገራል። . ሌላኛው እና እኔ ስያሜውን ለፌስቡክ ስም ለማድረግ መነሻ ምክንያቱ ደግሞ የደጅ አዝማች ገልሞ ጓንጉል የፈረስ ስም ስለሆነ ነው። ትንሽ ማብራሪያ ለመሰጠት ያክል ዛሬ ድረስ ከመርሳ ከተማ ጋር ተያይዞ ስማቸው ጎልቶ የሚታወቀው ሼኹ አባ ጌትየ ወደ 48 በላይ ልጆች ነበራቸው። . ከእነዚህ መካከል ዝነኛና ታዋቂ የነበሩት እና ክርስትናም ተቀብለው የፈረሳቸው እግር የረገጠበትን ሁሉ እንዲገዙ በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ በዳግማዊ ዓጤ እያሱ የተሾሙት አባ ሴሩ ጓንጉል (ጓንጉል አበየ) ናቸው። ጓንጉል በፈረስ ስማቸው አባሴሩ በመባል ነው የሚጠሩት። በፈረስ ስም የመጠራትን ባሕል ለኢትዮጵያ ነገሥታት ያወረሱት የወረሴህና የማመዶች ሥርወ መንግስታት መሳፍንቶች ናቸው ተብሎ ይታመናል። . አባሴሩ ጓንጉል የታወቁ ፈረሰኛ እና መልከ መልካም የሚያምሩ ሰው እንደ ነበሩ በትውፊት ሰምተናል። በተለያየ ጊዜ በርካታ ሚስቶችን አግብተው ከ20 በላይ ልጆችን ወልደዋል። ሚስቶቻቸው ከአምባሰል፣ ከላስታ፣ ከራያ፣ ከየጁ ከቃሊምና ሀብሩ ወዘተ አካባቢወች ነበሩ። አባ ሴሩ ጓንጉል አምባሰልን ጨምሮ ዛሬ ሰሜን ወሎ የሚባለውን አካባቢ እስከ ጨጨሆ በር ድረስ የገዙ ናቸው። . ጓንጉል ከራያ ጉራ ወርቄ ያገቧት ሚስታቸው ወይዘሮ ራጂያ ትባል ነበር፣ ከላስታ ያገቧት ደግሞ ወይዘሮ ገለቡ ፋሪስ ትባል ነበር። ወይዘሮ ገለቡ የላስታው ገዥ የራስ ፋሪስ እህት ነች እያሉ የጻፉ ስወች ቢኖሩም፤ እውነታው ግን የራስ ፋሪስ ልጅ ናት የሚለው ነው። ጓንጉል አባሴሩ ክርስትያን ቢሆኑም የታወቁት የሼኹ አባጌትየ ልጅ በመሆናቸው እስላማዊ ልማዶችና ትውፊቶች በቤታቸው የሚስተዋል ነበር፤ አኗኗራቸውም እንደ ሙስሊም ነበር ይባላል። የላስታው የራስ ፋሪስ ልጅ የሆነችው ባለቤታቸው ወይዘሮ ገለቡ የባሏ ቤተሰቦች የሆኑት ሼኾቹ በቤቷ ዱዐ ሲያደርጉ ጥሩ ሙሪድ ነበረችና በደምብ አድርጋ ስለምትካድማቸው በሼኾቹ ተወዳጅ ነበረች። የጉራ ወርቄዋ ባለቤታቸው ወይዘሮ ራጂያ ደግሞ፤ በሼኾቹ ተመራጭም ተወዳጅም አልነበረችም። ታዲያ ሼኾቹ የጓንጉል ዘመዶች አንድ ቀን በዱዐ መሀል ሀድራው ሲግል . ራጂያ ራጂያ ወለደች አህያ አህያ ገለቡሳ ገለቡሳ ወለደች አምበሳ አምበሳ . በማለት ዋሪዳው በሉ ያላቸውን ብለው ገለቡን በቱፍታቸው አዳረሷት አሉ። መቼም የወረሴሆች ታሪክ ከመዐና ጋር የተያያዘ ነውና የሼሆቹ ዱዐ ሰምሮ ከወ/ሮ ገለቡ የተወለዱት የአባ ሴሩ ልጆች እነ ራስ ቢትወደድ ቀዳማይ ዓሊ ጓንጉል፣ እነ ራስ ቢትወደድ ዓሊጋዝ ጓንጉል፣ የልጅ ልጆቿ እነ ራስ ቢትወደድ ጉግሣ መርሶ የጎንደርን ቤተ መንግስት ተቆጣጥረው፣ ከ65 ዓመት በላይ ማዕከላዊ መንግስትን በበላይነት እየመሩ፣ የፈለጉትን እያነገሡ ያልፈለጉትን እያወረዱ አድራጊ ፈጣሪ ሆነው የዚያኔዋን ኢትዮጵያ ገዙ። ከወ/ሮ ራጂያ የተወለዱት እነ ደጃዝማች ወሌ ጓንጉል፣ እነ ደጃዝማች ገልሞ ጓንጉል ገዥነታቸው በአካባቢያቸው የተወሰነ በመሆኑ በየጁ፣ ራያ እና ላስታ ብቻ አልፈው አልገዙም። . በተለይ የአባ ሴሩ ጓንጉል ወራሽ ይሆናል የተባለው የደጃዝማች ወሌ የአምበሳ ደቦል ካላመጣችሁ እያለ ሕዝብ የሚያስቸግር ተንኮለኛ ነበረና መጨረሻው የማያምር ነበር። የደጃማች ወሌ ወንድም የወይዘሮ ራጂያ ልጅ የደጃዝማች ገልሞ ጓንጉል የፈረስ ስሙ አባቦና ይባላል። ደጃዝማች ገልሞ ጓንጉል በተለምዶ በዜና መዋዕልም ጭምር <አባቦና ገልሞ> እየተባለ ነበር የሚጠራው። ቦና በዚህ አገባብ ትርጉሙ <ኩራት> ማለት ነው።

#ዋለልኝ መኮንን ካሳ ኩራሽ ጅማ ማነው?

ዋለልኝ መኮንን ካሳ ኩራሽ ጅማ ማነው? 1. ትውልድና እድገቱ በከፊል ዋለልኝ መኮንን የተወለደው መጋቢት 11 ቀን 1938 ዓ.ም ደቡብ ወሎ ቦረና ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ሲሆን የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደሴ ከተማ በሚገኙት ስመ ጥሮቹ ንጉስ ሚካኤልና ወይዘሮ ስህን ትምህርት ቤት ተከታትሏል። የ12ኛ ክፍል ትምህርቱንም ያጠናቀቀው በ 1958 ዓ.ም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ስር ይተዳደር በነበርው በልዑል በዕደማርያም ቅድመ ዝግጅት ትምህርት ቤት (Preparatory School) ውስጥ ነበር። በዚህ ትምህርት ቤት ቆይታው በሥነ ፅሁፍ ዝግጅት የላቀ ሚና ተጫውቷል። የክርክር ክበብ ምክትልና ዋና ፕሬዝዳንትም በመሆን አገልግሏል። በዚሁ ክበብ አማካኝነት በተለይም የሥነ አመክኗዊ ውይይት አካሄድን ልቅም አድርጐ እንደተማረ ይነገርለታል። ትምህርት ቤቱ ዋለልኝን ተከራካሪ ብቻ ሳይሆን ጥሩ ፀሃፊም እንዲሆን ረድቶታል። በሁለት ዓመት ቆይታው የትምህርት ቤቱ የጋዜጣ ረዳት አዘጋጅ በመሆንም አገልግሏል። ዋለልኝ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ በቀድሞ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ በ Political Science የትምህርት ክፍል ትምህርቱን ቀጥሏል። ከዚያም በኋላ በ ሕዳር 18, 1961 ዓመተ ምሕረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በተደረገው የሥነ ጽሁፍ ውድድር ኢትዮጵያውያን ከጣሊያን ወታደር ጋር ያደረጉትን ተጋድሎ፣ መስዋዕትነት፣ ጀግንነት፣ ለአገር ታማኝነትና ፍቅርን የሚያሳይ ሰነ ጽሁፍ ጽፎ ከተወዳዳሪዎቹ ውስጥ የአንደኝነት ማዕረግ በመጐናጽፉ ሽልማት አግኝቷል። በየዓመቱ በሚከበረው የዩኒቨርሲቲው ቀን ላይም በመወዳደር ካሸነፉት ስመጥር ገጣሚዎችና ባለቅኔዎች አንዱ ነበር። .ዋለልኝ መኮንን ካሳ ኩራሽ ጅማ ማነው? ውሎ የከረዩ ልጅ ነው፡፡ የባሬንቱ የልጅ ልጅ፡፡ ከከረዩ ልጆች መካከል ባሶና ዱለቻም ይገኙበታል፡፡ ዱለቻ ውስጥ እነ ሊበን አሉ፡፡ ሰባት ቤት ወሎ፡- ወረ ኢሉ፣ ወረ ሂማኑ፣ ወረ ባቦ፣ ወረ ቃሉ፣ለገ ሂdhaa፣ ለገ ጎራ እና ለገ አምቦ ናቸው፡፡ ከከረዩ ልጆች ወሎን አልፈው ጎንደር ድረስ የሄዱት ሊበኖች ናቸው፡፡ ሊቦ ከመከምን ፡፡ ከመ ከም “Warra Akkam akkam jedhu” “እንዴት እንዴት ነው? የሚሉት” ፡፡ የጃዊ ሽመል የሚባሉትን ሎጋዎችም፡፡ ጎጃም ባሶ ሊበን ወረዳ አለ፡፡ በተሻለ ጥበቡ መጽሀፍ የጎጃም አዛውንቶች “Gojam ጋ* ነው” ይላሉ ሲል ደምድሟል፡፡ ወሎ ያለው ሜታ በደራ በኩል የተሻገረው ቡድን ነው፡፡ ደራ ደግሞ ዋጂቱ ነው፡፡ የበቾ ዋጂቱ ኦሮሞ፡፡ ደራ “አደሬ ዋጂቱ” የሚባል ገበያ አለ፡፡ “አደሬ” ማለት ገበያ ማለት ነው፡፡ ትንሽዬ ገበያ፡፡ እነሱ "ሚዳ ኦረሞ" በማለት የሚጠሩት ዋጂቱዎች ናቸው፡፡ ) . የዋለልኝ አባት የሜታ ኦሮሞ ናቸው፡፡ መኮንን ካሳ ኩራሽ ጅማ፡፡ አስራ ሶስተኛ ትውልዱ “ጭላሎ” ነው፡፡ በእናቱም እንዲሁ “ኛአ”የሚል ስም አለ፡፡ደራሲ አለማየሁ ኀይሌ እስከ 13 ትውልዱ መዝግቧል፡፡ 2. የተማሪዎች ንቅናቄ ላይ የነበረው ተሳትፎ ዋለልኝ መኰንን በዩኒቨርስቲ ቆይታው የኢትዮጵያን አርሶ አደሮችና ላብ አደሮች ነፃ ለማውጣት በ1960ዎቹ ውስጥ በተደረገው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ትግል ውስጥ ዓብይ ሚና የተጫወተ ወጣት ነበር። ጥላሁን ግዛው የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ ከተመረጠ በኋላ ባደረገው ከፍተኛ የትግል ተሳትፎ ከባድ ክትትል ይደረግበት ነበር። አፍንጮ በር አካባቢ ታህሳስ 19, 1961 ዓ.ም ጥላሁን ግዛው በጥይት ይመታል። ይህ አሳዛኝ ሁኔታ ሲፈጠር ዋለልኝ መኰንን አምስት ኪሎ አካባቢ በሚገኘው ቤቱ ከጓደኞቹ ጋር ነበር። አንድ ወጣት ወደ ቤት ይመጣና ስለ ጥላሁን ግዛው በጥይት መመታት ይነግራቸዋል። እነሱም በድንጋጤ ተያይዘው ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ይሄዳሉ። ሐኪሞቹ ሕይወቱን ለማትረፍ ሞክረው እንዳልተሳካላቸው ይነግሯቸዋል። በዚህ ወቅት ዋለልኝና ጓደኞቹ የጥላሁንን አስከሬን ከሆስፒታሉ በመውሰድ ዩኒቨርስቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ በስርዓት ያስቀምጡታል። ከዚያ በኋላ የተቃውሞ ትዕይንትና የቀብሩን ሥርዓት ዝግጅት ያደርጋሉ። ለኮሌጅና ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መልዕክቶችን ያስተላልፋሉ። የጥላሁን ሞት ትግላቸውን እንደማይገታው፣ ጥላሁን ቢሞት ሽህ ጥላሁኖች እንደሚፈጥሩ በመግለጽ ጽሁፎችን በሕዝብ መሃል ያሰራጫሉ። በዩኒቨርስቲው ውስጥ ያለውን የጥላሁንን አስከሬን ለመውሰድ ወታደሮች በዩኒቨርስቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ይገባሉ። በዚህ አጋጣሚ ዋለልኝ ከፎቅ ላይ ሆኖ በድምፅ ማጉያ ጥላሁንን የሚቀብሩት የትግል ጓዶቹና ሕይወቱን የከፈለለት ሕዝብ እንጂ ገዳዮቹ መቅበር እንደማይችሉ ይናገራል። የክብር ዘበኛ ወታደሮች በተማሪዎቹ ላይ ተኩስ ከፍተው አበበ በርሔ፣ ስብሃቱ ውብነህ፣ ጀማል ያሲን የተባሉ ሶስት ተማሪዎችን ይገላሉ። በዚያ ሽብር ወቅት ዋለልኝ መኰንን ይተርፋል ያለ ሰው አልነበረም። ነገር ግን ዋለልኝና ጓደኞቹ ኮልፌ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማሰልጠኛ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይታሰራሉ። ዋለልኝ ከአሁን በፊት በገደብ ስለተለቀቀ እንደገና ወደ ከርቸሌ እስር ቤት ይላካል። ዋለልኝ መኰንን ከእስር ቤት ከተለቀቀ በኋላ ወደ ትምህርቱ እንዳይመለስ ታገደ። 3. የዋለልኝ የብሔረሰቦች ጥያቄ በኢትዮጵያ ፅሁፍ (Walelign On the question of nationalities in Ethiopia) ዋለልኝ መኮንን ይህንን አወዛጋቢና ዝነኛ የሆነ አጭር ፅሁፍ “ታገል” (Struggle) ተብሎ በሚታወቀው የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መፅሄት ላይ ሲያወጣ ገና የ 24 ዓመት ወጣትና በዩኒቨርስቲው ደግሞ የ4ኛ አመት የ (Political Science) ተማሪ ነበር። በዚው ፅሁፉ ውስጥ ዋለልኝ እልል ያለ ማርክሲስት (Marxist) እንደነበረና በኢትዮጵያ ውስጥ አለ ብሎ ያመነው “የብሄረሰቦች ጭቆና” በተባበረ የህዝብ አመፅና (Popular Armed Violence) በሶሻሊስት ፖለቲካዊ ርዮተ-አለም (Socialist Political Ideology) ብቻ ሊፈታ እንደሚችል በግልፅ አስቀምጧል። ብሄራዊ ጭቆናውን ለማስረዳት ኢትዮጵያዊ ማን ነው? የሚል የዜግነት ጉዳይና ኢትዮጵያ ከምን ከምን ነው የተሰራችው ? የሚሉ መሰረታዊ ጥያቄዎችን አንስቷል። "What are the Ethiopian peoples composed of? I stress on the word peoples because sociologically speaking, at this stage, Ethiopia is not really one nation. It is made up of a dozen nationalities with their own languages, ways of dressing, history, social organization and territorial entity. And what else is a nation? It is not made of a people with a particular tongue, particular ways of dressing, particular history, particular social and economic organization? Then, may I conclude that, in Ethiopia, there is the Oromo Nation, the Tigrai Nation, the Amhara Nation, the Gurage Nation, the Sidama Nation, the Wellamo [Wolayta] Nation, the Adere [Harari] Nation, and however much you may not like it, the Somali Nation.” ከዚያም በመቀጠል የመፍትሄ ሃሳቦች ያላቸውን በወቅቱ ሲደረጉ ከነበሩት የፖለቲካ ትግሎች ጋር እያዛማደ ለማስረዳት ይሞክራል። ለምሳሌ ስለ መፈንቅለ መንግስት ያነሳና፤ መፈንቅለ መንግስት ቢካሄድ የታሰበውን ለውጥ እንደማያመጣ ይልቁንም ሃገሪቱን ወደ ባሰ ችግር ውስጥ ሊከታት እንደሚችል ይገልፃል። “Can we do it through military? No!! A military coup is nothing more but a change of personalities.” በመቀጠልም በወቅቱ ይደረጉ ስለነበሩት የጎጃምና የባሌ አመፆች ያነሳና አስፈላጊነታቸውን አምኖና ተቀብሎ ነገር ግን የመጨረሻ ግብ የላቸውም ብሎ ያልፋቸዋል። “Can the Eritrean Liberation Front and the Bale armed struggle achieve our goal? Not with their present aims and set-up. Both these movements are exclusive in character, led by the local Bourgeoisie in the first instance and the local feudal lords in the second.” “. . . The same can be said for the Gojjam uprising.” ሌላው ዋለልኝ በዚው ፅሁፉ ውስጥ ያነሳው፤ በአሁኑ ወቅት በኢፌዴሪ ሕገ-ማንግስት አንቀፅ 39 በግልፅ የተቀመጠዉን “የራስን እድል በራስ የመወሰን ብሎም እስገመገንጠል” የሚለውን ሀረግ ነው። ዋለልኝ ሲገልፀው እንዲህ ይላል፤ “There is nothing wrong with secessionism as such. For that matter secession is much better than nationally oppressive government. I quote Lenin, “…People resort to secession only when national oppression and national antagonisms make joint life absolutely intolerable and hinder any and all economic intercourse. In that case the interests of the freedom of the class struggle will be best served by Secession.” በመጨረሻም ዋለልኝ ፅሁፉን ወደ ማጠቃለሉ ሲመጣ How can we form a genuine egalitarian national-state? a genuine Nationalist Socialist State? ሲል ጥያቄ ያቀርባል። ለጥያቄውም መልስ ሲሰጥ “It is clear that we can achieve this goal only through violence, through revolutionary armed struggle.” ብሎ ይደመድማል። 4. የዋለልኝ ያልተሳካው ያውሮፕላን ጠለፋ ዋለልኝ መኰንን፤ የጥላሁን ግዛውን መገደል ተከትሎ በተነሳው አመፅ ዋና ተሳታፊ ስለነበር ታስሮ ከርሟል። ከዛም በተጨማሪ “የአዋጁ አዋጅ” የሚል አፄ ሀይለስላሴ የተማሪዎችን እንቅስቃሴ አስመልክቶ የተቃወሙብትን ንግግር የሚያጣጥል ፅሁፍ በመፃፉ ምክንያት የከፍተኛው ፍርድ ቤት አምስት አመት ፈርዶበት ነገር ግን አፄው በሴራ ለማስገደል ባደረጉለት ይቅርታ ከሶስት ወር እስራት በኋላ ከእስር ሊፈታ ችሏል። ዋለልኝ ከእስር ቤት ከተለቀቀ በኋላ የተማሪዎቹ ልሳን የነበረው ታገል መጽሄት ታገደ እሱም እንደዚሁ ከትምህርት ቤቱ ታገደ። ከዚያ በኋላ፤ በወቅቱ የመንገድ ማመላለሻ አስተዳደር ተብሎ ይጠራ በነበረው መንግሥታዊ ድርጅት ሥራ መስራት ጀመረ። በዚሁ ድርጅት ሥራ እየሰራ እያለ ብርሃነ መስቀል ረዳና (የኢሃፓ መስራችና ካዛ አስቀድሞ አውሮፕላን ጠልፎ ከሃገር የወጣ) ሌሎች የትግል ጓዶቹ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ድርጅት መሥራች ጉባዔ ስብስባ በርሊን ላይ በመጥራታችው ፤ ዋለልኝም በዚህ ስብስባ ላይ ለመገኘት ወሰነ። ወደ ስብሰባው ለመቀላቀል አውሮፕላን ከመጥለፍ ሌላ አማራጭ አልነበረውም። ሕዳር 29, 1965 ዓመተ ምሕረት ከጥዋቱ አንድ ስዓት ተኩል ላይ ከአዲስ አበባ ተነስቶ (በአሥመራ በኩል ወደ አቴንስ ሮም ፓሪስ) ለመሄድ የተነሳውን የበረራ ቁጥር 708 ቦይንግ ጄት አውሮፕላን፣ ዋለልኝ መኰንን፣ ማርታ መብራቱ (በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የሕክምና ተማሪ የነበረች)፣ታደለች ኪዳነ ማርያም (በማስታወቂያ ድርጅቶች ትሰራ የነበረች)፣ አማኑኤል ዮሐንስ (የዩንቨርሲቲ ተማሪ የነበረ)፣ ጌታቸው ሀብቴ (የዩንቨርስቲ ተማሪ የነበረና ከውጭ ሃገር ጋዜጠኞች ጋር ይሰራ የነበረ)፣ ፣ ዮሐንስ ፈቃዱና (የዩንቨርስቲው 4ኛ አመት ተማሪ የነበረ) ተስፉ ቢረጋ (በመድሐኒያለም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ያስተምር የነበረ) ሊያስገድዱት ሞክረው ባለመሳካቱ ታደለች ኪዳነ ማርያም ስትተርፍ ዋለልኝ መኰንን እና ሌሎቹ በአውሮፕላን ውስጥ በጸጥታ አስከባሪዎች በተተኮሰ ጥይት አየር ላይ ሕይዎታቸው አለፈ። በመጨረሻም የዋለልኝ መኮንን ቤተሰቦች አባቱን ጨምሮ አስክሬኑን ከምኒልክ ሆስፒታል ተቀብለው ከአዲስ አበባ አገሩ ወሎ ተወስዶ በደሴ ከተማ መድሃኒዓለም ቤተክርስትያን ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት በተወለደ በ27 ዓመቱ በክብር ተቀብሯል።

Saturday, February 12, 2022

#Abay-#አባይ(አባያ) በ #ሎሬት ፀጋዬ ገ/ መድሕን ሮበሌ ቀዌሳ

~~~~~አበያ (አባይ)በሎሬት ፀጋዬ ሮበሌ ቀዌሳ~~~~~ አባይ የማን ነበር? አሁንስ የማነው? ኦሮሞ(የኩሽ ታላቅ ልጅ) እና አባይ የነበራቸው ቁርኝት ምን ይመስል እንደነበር ሎሬት ፀጋዬ ሮበሌ ቀዌሳ በሚገርም መልኩ በብዕሩ ከትቦልን አልፏዋል። 🌲 🌲 🌲 🌲 🌲 አባይ የምድር አለም ሲሳይ የቅድመ-ጠቢባን አዋይ አባይ የጥቁር ዘር ብስራት የኢትዮጵያ ደም የኩሽ እናት የዓለም ስልጣኔ ምስማክ ከጣና በር እስከ ካርናክ በጡትሽ እቅፍ እንዲላክ ለራህ ለፀሐዩ ግማድ ፥ ለጣህ ለክዋክብት አምላክ ከጥንተ-ፍጡራን ጮራ ፥ የመነጨሽ ከኩሽ አብራክ። አባይ የምድረ-ኩሽ መኩሪያ በቅደመ-ታሪክሽ ጥርጊያ ከደም-ቢያ እስከ ኑ-ቢያ ከሜምፊስ እስከ ሜሮኤ በስልጣኔሽ ትንሳኤ ከዴልታሽ እስከ ዴር-ሡልጣን ከኡመ-ራህ እስከ ኡመ-ዱርማን፤ አባይ የአቴስ የጡቶች ግት ለዓለም የስልጣኔ እምብርት፤ ጥቁር አባይ የጥቁር ምንጭ የካም የስልጣኔ ምንጭ፤ አንቺ የምድረ ዓለም ሲሳይ በረሃውን ጥለሽ ግዳይ ሰሃራን እንዳክርማ ተልም ሰንጥቀሽው በወዝሽ ደም ፥ በጥበብሽ ስርወ-ፋና አንቅተሽ በአንቀልባሽ አዝለሽ ፥ የቅድመ ታሪክን ዝና የራምሴስን አበ-ሲምቦል፥ የመነስን ልዕልና በአልፋ የአልሙጋን ሐውልት፥ የቢያ-ሃንኬን ፍልስፍና በኮማምቦ የሶባቃን፥ በናፖታም የኤዛና ፊላኤ የአቴሰን ምኩራብ፥ በልቅጾር የአሞንን ዜና፤ አባይ ታላቅ ቅድመ-ተስፋ የኪነት ጉባኤ አልፋ፥ ረቂቅ አባይ ያንቺ መገን ምጥቀትሽ አይተንተን፥ የእጅ ማስነሻሽ በረከት ግብርሽ ከአድማሳት ሲክትት መንጣለያሽ ከዕለት ዕለት መሻገሪያሽ ካመት-አመት በመስዋዕት ሲወድቅልሽ በዝማሜ ሲፈስልሽ በመመለክ በመመስገን ጽላትሽ ከዘመን ዘመን በአዝርእት አበቅቴሽ ሲታጠን አቤት አባይ ላንቺ መገን አባይ ረቂቅ የጠቢብ ዘንግ የጨረቃን ጉዞ ፈለግ አስቀምረሽ በጠቢብ ዘንድ በፍሳሽሽ ውጣ ውረድ በሙላት ሚዛን ረገድ የሰማይን ጥርጊያ መንገድ ፥ የጊዜ መለኪያ ሰዓት ፥ ዜኒት ባንቺ ተቀምራ ከቴቤስ እስከ ዳንዳራ ብስራትሽን እንደደመራ ሥልጣኔሽ አንዳበራ፥ የመጽሐፈ-ሙታን ዜና አድርጎሽ ቅድመ-ገናና ዛሬ ወራቱ ራቀና ምድረ-ዓለም ያንቺን አድናቆት ፈለጉን መሻት ተስኖት እንዲህ ባንቺ መንከራተት ታሪክ ወሮታሽ ጠፍቶበት ትላንት በባዕድ ጩኸት ዛሬም ባላዋቂ ሁከት ቋንቋ ለቋንቋ ቢራራቅ የቅድሚያሽ ንድፍ ላይፋቅ እዚህ ደሜም እዚያ ተማም መባልሽ ብቻ ባይበቃም የቅርስሽ ጭብጥ ይዞታ ሆሄታሽ እስካልተፈታ፥ አባይ ፋናሽ የሕልም ርቅ ፈለግሽም ቢሆን ደቂቅ እንዴት እንዴት ነበር ብለን ካልደረስንበት ፈልፍለን፥ የጥንቷ አባይ እንዴት ትሆን አባይ-አቢይ አባይ-ግዮን ከምንጩ የጥበብ ሳሎን ግሪክ ፋርስና ባቢሎን ጭረው በቀዱበት ሸሞን፥ አባይ የአማልክት አንቀልባ የቤተ-ጥበባት አምባ ከኩሽ የቅድመ-አበው ብሁል ከተራራሽ አናት ቁልቁል የሰው ዘር የታሪክ-ፊደል ፥ ገና ከፅንሱ ሲረቀቅ ሲሳይም የእትብቱን ቆባ፥ ምጥቀቱን ለማንፀባረቅ ዘለዓለሙን ለማሳወቅ እስከሜዲትራኒያ፥ ጢሰ እሳትሽ ሲፍለቀለቅ፥ አባይ-አብይ ፥ አባይ ግዮን ለአማልክቶች አምላክ ለአሞን የኪነት ምንጩ እምትሆን፤ ለኦሩሰ ርቱእ አክናፋት ለነዳዮናይሶስ አባት ከእምብርትሽ የፀሐይ አምላክ ፥ ተቀስቶ በሰማያት ያረበበብሽ እንደ እሳት፤ ጥቁር አባይ ነጥቁር ምንጭ የካም የስልጣኔ ፍንጭ የቅድመ ታሪክሽ ጥርጊያ ከደም-ቢያ እስከ ኑ-ቢያ፥ የኢትዮጲስ ደም የኩሽ እናት አባይ የጥቁር ዘር ብስራት የዓለም ስልጣኔ ምስማክ ከጣና በር እስከ ካርናክ በጡትሽ እቅፍ እንዲላክ ለራህ ለፀሐዩ ግማድ፥ ለጣህ ለከዋክብት አምላክ፤ ከጥንተ-ፍጡራን ጮራ፥ የመነጨሽ ከኩሽ አብራክ፤ ሰሃራን እንደምሁር ተልም ያለመለመሽ በወዝሽ ደም የቅድመ-ጠቢባን አዋይ አባይ የምድር ዓለም ሲሳይ። ተነስ ንቃ አስመልስ ንገስ... ባላምባራስ ነጋሽ Negash Qemant~~~~~አበያ (አባይ)በሎሬት ፀጋዬ ሮበሌ ቀዌሳ~~~~~ አባይ የማን ነበር? አሁንስ የማነው? ኦሮሞ(የኩሽ ታላቅ ልጅ) እና አባይ የነበራቸው ቁርኝት ምን ይመስል እንደነበር ሎሬት ፀጋዬ ሮበሌ ቀዌሳ በሚገርም መልኩ በብዕሩ ከትቦልን አልፏዋል። 🌲 🌲 🌲 🌲 🌲 አባይ የምድር አለም ሲሳይ የቅድመ-ጠቢባን አዋይ አባይ የጥቁር ዘር ብስራት የኢትዮጵያ ደም የኩሽ እናት የዓለም ስልጣኔ ምስማክ ከጣና በር እስከ ካርናክ በጡትሽ እቅፍ እንዲላክ ለራህ ለፀሐዩ ግማድ ፥ ለጣህ ለክዋክብት አምላክ ከጥንተ-ፍጡራን ጮራ ፥ የመነጨሽ ከኩሽ አብራክ። አባይ የምድረ-ኩሽ መኩሪያ በቅደመ-ታሪክሽ ጥርጊያ ከደም-ቢያ እስከ ኑ-ቢያ ከሜምፊስ እስከ ሜሮኤ በስልጣኔሽ ትንሳኤ ከዴልታሽ እስከ ዴር-ሡልጣን ከኡመ-ራህ እስከ ኡመ-ዱርማን፤ አባይ የአቴስ የጡቶች ግት ለዓለም የስልጣኔ እምብርት፤ ጥቁር አባይ የጥቁር ምንጭ የካም የስልጣኔ ምንጭ፤ አንቺ የምድረ ዓለም ሲሳይ በረሃውን ጥለሽ ግዳይ ሰሃራን እንዳክርማ ተልም ሰንጥቀሽው በወዝሽ ደም ፥ በጥበብሽ ስርወ-ፋና አንቅተሽ በአንቀልባሽ አዝለሽ ፥ የቅድመ ታሪክን ዝና የራምሴስን አበ-ሲምቦል፥ የመነስን ልዕልና በአልፋ የአልሙጋን ሐውልት፥ የቢያ-ሃንኬን ፍልስፍና በኮማምቦ የሶባቃን፥ በናፖታም የኤዛና ፊላኤ የአቴሰን ምኩራብ፥ በልቅጾር የአሞንን ዜና፤ አባይ ታላቅ ቅድመ-ተስፋ የኪነት ጉባኤ አልፋ፥ ረቂቅ አባይ ያንቺ መገን ምጥቀትሽ አይተንተን፥ የእጅ ማስነሻሽ በረከት ግብርሽ ከአድማሳት ሲክትት መንጣለያሽ ከዕለት ዕለት መሻገሪያሽ ካመት-አመት በመስዋዕት ሲወድቅልሽ በዝማሜ ሲፈስልሽ በመመለክ በመመስገን ጽላትሽ ከዘመን ዘመን በአዝርእት አበቅቴሽ ሲታጠን አቤት አባይ ላንቺ መገን አባይ ረቂቅ የጠቢብ ዘንግ የጨረቃን ጉዞ ፈለግ አስቀምረሽ በጠቢብ ዘንድ በፍሳሽሽ ውጣ ውረድ በሙላት ሚዛን ረገድ የሰማይን ጥርጊያ መንገድ ፥ የጊዜ መለኪያ ሰዓት ፥ ዜኒት ባንቺ ተቀምራ ከቴቤስ እስከ ዳንዳራ ብስራትሽን እንደደመራ ሥልጣኔሽ አንዳበራ፥ የመጽሐፈ-ሙታን ዜና አድርጎሽ ቅድመ-ገናና ዛሬ ወራቱ ራቀና ምድረ-ዓለም ያንቺን አድናቆት ፈለጉን መሻት ተስኖት እንዲህ ባንቺ መንከራተት ታሪክ ወሮታሽ ጠፍቶበት ትላንት በባዕድ ጩኸት ዛሬም ባላዋቂ ሁከት ቋንቋ ለቋንቋ ቢራራቅ የቅድሚያሽ ንድፍ ላይፋቅ እዚህ ደሜም እዚያ ተማም መባልሽ ብቻ ባይበቃም የቅርስሽ ጭብጥ ይዞታ ሆሄታሽ እስካልተፈታ፥ አባይ ፋናሽ የሕልም ርቅ ፈለግሽም ቢሆን ደቂቅ እንዴት እንዴት ነበር ብለን ካልደረስንበት ፈልፍለን፥ የጥንቷ አባይ እንዴት ትሆን አባይ-አቢይ አባይ-ግዮን ከምንጩ የጥበብ ሳሎን ግሪክ ፋርስና ባቢሎን ጭረው በቀዱበት ሸሞን፥ አባይ የአማልክት አንቀልባ የቤተ-ጥበባት አምባ ከኩሽ የቅድመ-አበው ብሁል ከተራራሽ አናት ቁልቁል የሰው ዘር የታሪክ-ፊደል ፥ ገና ከፅንሱ ሲረቀቅ ሲሳይም የእትብቱን ቆባ፥ ምጥቀቱን ለማንፀባረቅ ዘለዓለሙን ለማሳወቅ እስከሜዲትራኒያ፥ ጢሰ እሳትሽ ሲፍለቀለቅ፥ አባይ-አብይ ፥ አባይ ግዮን ለአማልክቶች አምላክ ለአሞን የኪነት ምንጩ እምትሆን፤ ለኦሩሰ ርቱእ አክናፋት ለነዳዮናይሶስ አባት ከእምብርትሽ የፀሐይ አምላክ ፥ ተቀስቶ በሰማያት ያረበበብሽ እንደ እሳት፤ ጥቁር አባይ ነጥቁር ምንጭ የካም የስልጣኔ ፍንጭ የቅድመ ታሪክሽ ጥርጊያ ከደም-ቢያ እስከ ኑ-ቢያ፥ የኢትዮጲስ ደም የኩሽ እናት አባይ የጥቁር ዘር ብስራት የዓለም ስልጣኔ ምስማክ ከጣና በር እስከ ካርናክ በጡትሽ እቅፍ እንዲላክ ለራህ ለፀሐዩ ግማድ፥ ለጣህ ለከዋክብት አምላክ፤ ከጥንተ-ፍጡራን ጮራ፥ የመነጨሽ ከኩሽ አብራክ፤ ሰሃራን እንደምሁር ተልም ያለመለመሽ በወዝሽ ደም የቅድመ-ጠቢባን አዋይ አባይ የምድር ዓለም ሲሳይ። ተነስ ንቃ አስመልስ ንገስ... ባላምባራስ ነጋሽ Negash Qemant

#Miky _Sultan-Personal _history_

Miky[Mekin] sultan seid was born on 12 May 1996 in the Bati, Wollo Province bordering kallu. His father was wollo Oromo Worseh, of Muslim faith, while his mother was wara ruga Oromo, an sunni muslim; Miky began his formal education at a gerbi school in kemise and Bati Qarsa premieri school. He attended secondary school in Bati until 2010.

Thursday, February 10, 2022

#Artist Muhe_Abarraa_Walloo

#Muhe_Abarraa Walloo kamisee Aanaa dawaa caffaatti seensa bara 1950 keessatti dhalate. Muhee abarraa sagalee kiloolee isaa saniin xiqqummaa isaa irraa hanga dullumaatti, taphoota kanneen biyya tana keessatti beekamoo ta'an akka Bati major,Ambassal,Anchi hoyye,tizitaa taphachuudhan namni isa qixxaatu hin jiru ture. Artist muhee abarra walaleessaaf taphataa salphaa hin turre nama mana dhugaatii keessa deemee alkoolii dhuguuf maallaqa guurratu hin turre,nama safuuf aadaa ummata isaa eeggatee kiraarif,maasinqoon sagaleen taphatuudha. Muhee abarraa hiree ta'eeti iddoo hin beekamneti dhalateef malee artistoota biyyi tun sadarkaa guddaa kenniteefi ol nama sadarkaan kennamuufii qabuudha ture.muheen kennaa uumaatin, sagaleessaaf,kiraara taphachuun nami isa gitu inuma hin jirre ture.otoo akka warra ammayoomee kanatti sagaleen isaa studio galee waraabamee editor godhamee namni isa gitu hin jiru sadarkaa tokkoffaa irratti taa,aa ture. Artist muhe abarra nama Aadaa,afaan,gootummaa saba isaatii beeksisuudhaan nama kutatee ka,ee ummata isaa ittiin bohaarsaaf beeksisaa tureedha.artist muhe abarra kan beekamuu dhabaate naannoo biraatti waan hin beekaneef qofa dandeettiin isaa dhokatee hafe.waraabbiin sagalee isaatis teephi kaassetatti waan tureef baayyina yeroo keessa badaa dhufe. Akka hireetti ta,ee muheen dandeettii isaa san ka kiraariif,maasinqoo sagaleen taphachuu dandayu san osoon waraabamin hafe. Tapha isaa keessaa, kaaruwwaan tapha baayyee namatti tolu ture. / Balambaras Qimant irraa/ miky sultan..

Thursday, February 3, 2022

#Omotic,#Nilotic የምባሉ ሁሉ የኩሽ ቅርጫፍ ናቸው"

ኦሞቲክ ናይሎቲክ የሚባሉ ሕዝቦች 100% በመረጃ የተረጋገጠ የኩሽ ልጆች ናቸው ።ከ ኩሽ ያልተፈጠረ አንድም የ አፍሪካ ሕዝብ የለም። ሁሉም የ አፍሪካ ልጆች፣ Hortee kush ናቸው። መረጃው የደቡብ ሕዝቦች የጋምቤላና የቤንሻንጉል ሥምችና በግዛታቸው ውስጥ የሚገኙ የቦታ የቀበሌ የተራራ የወንዝ ሥሞች አብዛኞቹ ከኩሽ(Kement)ቃል የመጡ ናቸው። በሙሉ ከነትርጉሙ የኬሜንት ቃል ነው። ካምባታ ፤ ወልሃይታ፤ዋላሞ (ከሁለት አንዱ) ፤ኩሎ መኳኳል ፤ጥምባሮ ቀባጣሪ፤ አላባ ቆሊቶ የባንዲራ ተቀባይ ፤ቡርጂ የተደበረ ፤ዳራሳ ልብሱ፤ ማጂ ታህሣሥ፣ አዋሳ ማህበረሰብ ፤ኮንሶ ንቦች፤ አዲያ ነጫማ፤ ገለብ ግፈፈው ፤ዳዋሮ መዳወሪያ፤ ዳሌ ግራጨ፤ ጌድኦ/ጋዲኦ ማሠሪያ፤ ጋሞ ማሰቃያ ፤ጎፋ ማለት ነው። ገሙ ጎፋ የሚባለው ጎፋ የገሙ አባት በመሆኑ ነው። አዋሳ የጡሙጋ ፤ ጡሙጋ የባሬንቱ ኦሮሞ ልጅ ነው። የአዋሳ ከተማ ሥም ከዚህ ታሪካዊ ሥም የመጣ ነው። ጉራጌ ከጉራ የመጣ ሥም ነው። ጉራ የቦረና ኦሮሞ ልጅ ነው። ጉራ ሲጠብቅ ጥቋቁር ሲላላ ጆሮ ማለት ነው። የጉራጌ ጎሳ ጨቦ ማለት መሰበር፤ ማራቆ መረቃማ፤ምስቃና ጥቃቅን ፍጡር ፤ዋላኔ ቀለበ፤ ማለት ነው። ደቡቦች ብቻ ሳይሆኑ የጋምቤላና ቤንሻንጉል ሕዝቦች የ ኩሽ ጎሳ ናቸው። የቤንሻንጉል ጥንታዊ ሥም ሻንገላ ነበር። ትርጉሙ አምስት ጊዜ የሚገባ ማለት ነው።ሲዳሞ የቦራና ኦሮሞ ልጅ ነው። ቦረና ዋላጋ፣ ጨላባ ፣ጎሬ፣ ጎፋ ፣ሲዳሞ ፣አኒያ፣ ጋሪ፣ ጉራ፣ ጌራና ዳጬን ወለደ። ከወለጋ ጌራና አኒያ ዝርያ በስተቀር የቀሩት ደቡብ ሕዝቦች ናቸው። ኦሮሞ የደቡብ ሕዝቦች ዘር ማህጸን ለመሆኑ ተጨማሪ መረጃ የሚከተሉት ናቸው። ከላይ የተገለጹ ሥሞች በሙሉ ከኦሮሞ በስተቀር በሌላ ሕዝብ ቋንቋ ውስጥ አይገኙም ልተረጎሙ አይችሉም። የብሔረሰቦቹ ሥም ብቻ ሳይሆን በግዛታቸው ውስጥ የሚገኙ የቦታ የቀበሌ የተራራ የወንዝ መጠሪያ ሥሞች አብዛኞቹ ከአሮሞ ቃል የወጡ ናቸው። Website:-https://mikysultan.blogspot.com/ Youtube:-https://youtu.be/CdY1umekwpU Telegram:- t.me/Oromo_ geography

Wednesday, February 2, 2022

#ቅድስት፣ ሀገር፣ ኢትዮጵያ ምን ማለት ነው?

"ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ" ÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷ ደብተራ ሲያደነዝዝህ "ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ" ይልህና "የስሟ ትርጓሜ ምንድነው?" ስትለው አይጥ የዋጠች ድመት መስሎ ዝም ጭጭ ይላል። አንዳንዴም "በልሳነ ... ግዕዝ... " ይልህና ተወጃብሮ ተወጃብሮ አንተን አወዛግቦህ ላሽ ይላል። ጠበቅ አድርገህ ከያዝከው "ዘወር በል መናፍቅ" ብሎ ይሰድብህና ሊያሸማቅቅህ ይሞክራል። ÷ ቅድስት ሀገር ማለት የለማኝ መፈልፈያ መሆን ነው እንዴ? ልመና የቅድስና መገለጫ ነው እንዴ? ቅድስና ጉስቁልና ነው እንዴ? ቅድስት ሀገር ውስጥ ወንድሙን ወንድሙ ይገድለዋል እንዴ? ምግባር የለሽ ሃይማኖተኛነት የቅድስት ሀገር መገለጫ ይሆናል ወይ? ነው በገድልና በተዓምር ተራራ ያሳከልካቸውን ፖለቲከኞች 6 ክንፍ ተክለህላቸው ታቦት መቅረጽ ነው ቅድስና? ÷ አሁን ያሉት መለካዊያን ለአብይ አህመድ ታቦት መቅረጻቸው ይቀራል ብላችሁ ነው? እነ ቅዱስ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በቅርቡ ታቦት ይቀረጽላቸዋል የሚል ተስፋ አለኝ። ምንያቱም የቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መሪዋ ነው እና! ይደልዎ በከመ ይሠየም ቅዱስ ወይትወሀብ ስድስቱ አክናፍ ለዳንኤል ክብረት እስመ መራሂሃ ውእቱ ለኢትዮጵያ! ሃሃሃሃ! ÷ እነዚህ ደብተራዎች እንዲህ እየፃፉ ነው "ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ" እያሉ ጆሯችን ያበሸቀጡት። በውኑ ኢትዮጵያ ከሌላው ዓለም በተለየ ቅድስት ናት? አሜሪካስ? የሚገርመው የቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሠባኪዎች አብዛኛዎቹ የአሜሪካ ፓስፖርት ያላቸው ናቸው። እናባ ዘነዘና ሁሉ እዛ ማዶ ነው የሚሞሩት። ÷ የቅድስቷ ሀገር ልጆች በአረብ አገራት ተቀጥረው እየማቀቁ ይገኛሉ። ይሄም የቅድስና መገለጫው ሆኖ ይሆን? መሪዎቿ በደብተራዎችና በጠንቋዮች ተከበው በሰው ልጆች ላይ የፈለጉትን እያደረጉ ሕዝባቸውን የሚያዋርዱባት ሀገር ቅድስት ከተባለች እርሷ ነክሳ ያሳደደቻቸውን ልጆቿን ተቀብለው በሠላም የሚያኖሩት ሀገራት ምን ይባሉ? ልጆቿን የምትበላው ደም መጣጯ ሀገር ኢትዮጵያ ቅድስት ከተባለች ኢትዮጵያዊያንን በስደት ተቀብላ የምትንከባከበው ሱዳን ቅድስተ ቅዱሳት መሆን ሲያንሳት አይደል ÷ ለመሆኑ ኢትዮጵያ የምትባለው በደብተራ ተንኮል የጎበጠች ሀገር ቅድስት ናትን? ከአለም ሀገራት የረከሱት ሀገራት እነማን ናቸው? የጅምላ ፅድቅ አለ ወይ? የቅድስና መገለጫወቿ ምን ምን ናቸው? ÷ ደብተራ ያገነናት አገር ለዛም ሰው ሳይሆን ጋራውና ሸንተረሩ ቅዱስ ከሆነ ሰዎችን የሚያከብሩና በመከባበር የሚኖሩባቸው ሀገራት እንዴት የበለጡ ቅዱሳን አይሆኑም? ÷ ደብተራ ጠላውን ተጎንጭቶ በስካር ጆሮው ሲግል፡ አይኑ ሲፈጥ መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጥና በግሳቱ አቧራ ተከልሎ ማንበብ ይጀምራል። በረሃ የሚለውን ኢትዮጵያ እያለ ያነበዋል። ትንሽ ቆይቶም ኢትዮጵያ 44 ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጠቅሳለች እያለ ያላዝንብሃል። ታዲያ በዚህ ጊዜ ጌታቸው ረዳ በሚዲያ ብቅ ይልና "በመጽሐፍ ቅዱስ በመጠቀስ ቅድስና ካለ ሦሪያ ከ380 በላይ ተጠቅሳለች፡ ግብጽም ከዚያ በላይ" ብሎ ያሳርፍልኛል። ÷ እነዚህ የምላስ እንጂ የተግባር ክርስትናን የማያውቁ ደብተራዎች ኢትዮጵያን ቅድስት ብለው መጥራት የጀመሩት ከነ ይኩኖአምላክና ተክለሃይማኖት በኋላ መሆኑ ታውቋል። ነገሥታቱ በምድር በሚሠሯቸው ተግባራት እንዳይመዘኑ መለኮታዉ ሆነው ያርፋሉ። ደብተራዎችም ይሄን ይለፍፋሉ። ንጉሳቸውንም "ሥዩመ እግዚአብሔር" ይሉትና ማንም እንዳይቀናቀነው ያደርጉታል። "ሰማይ አይታረስ ንጉሥ አይከሰስ!" በሚል ድንቁርናችን ተቀብለን እንድንገዛ ይሰብኩናል። አንዳንዴም ቅዱስ ዘርዓያዕቆብ፡ ቅዱስ እከሌ ወዘተ እያሉ እንድንሰግድላቸው ይስልሰብኩናል። "ኢይንሰግድ ለአምላከ ነኪር" ስንላቸው ደግሞ ይገድሉናል። ÷ ለመሆኑ ደብተራው ኢትዮጵያ የሚለውን ቃል መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዴት ነው እንዲበዛላቸው ሲጥሩ የኖሩት? ይሄን ለማየት ኪንግ ጄምስ ቨርሽን የሚባለውን እንግሊዝና መዝሐፍ ቅዱስ ከእኛው ጋር ለማነፃፀር ሞክሬ ነበር። ብዙውን እነርሱ እንዲመቻቸው እያደረጉ አስተካክለዋል። ለምሳሌ #1ኛ መዝ. 73፥14 በአማርኛ እንዲህ ይላል፡ "አንተ የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብም ምግባቸውን ሰጠሃቸው።" እንግሊዝኛው ደግሞ "Thou breakest the heads of leviathan in pieces, [and] gavest him [to be] meat to the people inhabiting the wilderness." ታዲያ ኢትዮጵያ የሚለውን ቃል ከየት አመጡት። እንግሊዝኛው የሚለው "...በበረሃ ለሚሞሩ ሰዎች ሥጋ እንዲሆናቸው ሰጠሃቸው" ነውና። ÷ #2ኛ መዝ. 71፥9 እንዲህ ይላል፡ "በፊቱ ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ፡፡ ጠላቶቹም አፈርን ይልሳሉ።" እንግሊዝኛው ደግሞ እንዲህ ይላል፡ "They that dwell in the wilderness shall bow before him; and his enemies shall lick the dust." ታዲያ ኢትዮጵያ የምትለውን ቃል ከየት አመጧት? "...በበረሃ የሚኖሩት..." የሚለውን ኢትዮጵያ ብሎ መተርጎም ምን ማለት ነው? ኢትዮጵያ በረሃ ነበረች እንዴ? ÷÷ እንግዲህ "ቅድስት ሀገር" የሚሉት ደብተራዎች እንጂ መጽሐፍ አይደለም። ሲጀመር ኢትዮጵያ የሚለውን ሥያሜ ትርጉም ጭራሽ አያውቁትም። በማያውቁት ሀገር ስለሚኖሩ ዝም ብለው ነው የሚቀባዥሩት። ማስረጃ የላቸውም። የተደረተ የተሰረዘ ወግ ነው የሚጠርቁት። እንኳን "ኢትዮጵያ" የሚለውን የመንደራቸውን ስም እንኳ መተርጎም አይችሉም። ÷ ለመሆኑ ነብሰገዳይ እንዴት ብሎ ነው የሀገርን ቅድስና ሊሰብከን የሞክረው? ትንሽ ቆይቶ ደግሞ ባንዴራው ከሰማይ የወረደ ነው ብሎን ያርፋል። Website:-https://mikysultan.blogspot.com/ Youtube:-https://youtu.be/CdY1umekwpU Telegram:- t.me/Oromo_ geography

mootittii saba'a Queen of sheba

"Mootittii Saba'a""Queen sheba" ----------------------------------------------------------------- ★Miky Sultan Bar...